ብራና ሚዲያ BRANA MEDIA
361 subscribers
1.3K photos
11 videos
146 files
169 links
Download Telegram
Add...
ብራና መጽሐፉ BRANA BOOK
በዚህ ግሩፕ ላይ ቢሳተፉ የምትሏቸውን Add ያድርጉ....
MIKIYAS DANAIL:
፨የብራና መጽሐፉ BRANA BOOK፨
®ዓላማ፦
1,ያነበብናቸውን መጽሐፉ የምንጠቁምበት
2,ካነበብናቸው መጽሐፉ ውስጥ ገዢ ሀሳቦችን። የምንለዋወጥበት
3,ነባር እና አዳዲስ የታተሙ መጽሐፉ የምንጠቁምበት።
4,በአጠቃላይ ስለመጽሐፍ የምንወያይበት ነው።
*የንስሐ መንገዶች (በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)*

አምስት የንስሃ መንገዶች አሉ ። የተለያዩ ቢሆኑም ቅሉ ሁሉም የሚያደርሱት ግን ርስት መንግስተ ሰማያት ነው ። እነርሱስ ምን ምን ናቸው ? ያልከኝ እንደሆነ እንድህ ብየ እመልስልሃለሁ፦

፩ኛ • የመጀመሪያው መንገድ "የራስን ኃጢአት ማመን፣ መጥላትና ማውገዝ ነው።

ይኽውም ልዑል ቃል ኢሳይያስ "እንድትጸድቅ መጀመሪያ ኃጢአትህን ተናገር እንዳለው" (ኢሳ 43 ፥26 )፤ ክቡር ዳዊትም "በደሌን አልሸፈንኩም፤ ለእግዚአብሔር መተላለፌን እንግራለሁ አልሁ ፤ አንተም የልቤን ኃጢአት ተውኽልኝ" ብሎ እንደተናገረ መዝ 31፥5 ስለዚህ አንተም ስለ ሰራኽው ኃጢአት እራስህን ውቀሰው። በዚህ እግዚአብሔር ይቅር እንዲልህ ታደርገዋለህና። ይህ ብቻ ሳይሆን ስለ ኃጢአቱ እራሱን የሚወቅስና ኃጢአቱን የሚኮንን ሰው በተመሳሳይ ኃጢአት በቀላሉ አይወድቅምና። ስለዚህ በጌታ የፍርድ ዙፋን የሚወቅስህ እንዳይኖር ዛሬ እውነተኛ ወቃሽ በኾነው ሕሊናህን አንቅተህ በራስህ ላይ ወቃሽና ከሳሽ አድርገህ ሹመው። ይህ አንዱና ደገኛው መንገድ ነው ።

፪• ሁለተኛው የንስሐ መንገድ ደግሞ
የወገኖቻችንን በደል ይቅር ማለትና በበደሉህ ላይ ቅሬታና ቂም አለመያዝ ነው።

እንዲህ ስናደርግ "ለሰወች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ እናንተንም ደግሞ ይቅር ይላችኋል" እንዲል እኛ በጌታችን ላይ ያደረግነውን በደል ይቅር እንባላለንና። ማቴ 6 ፡14

፫• ሦስተኛውን የንስሃ መንገድ መንበረ ጸባዖት የደርስ በትጋትና በጥልቅ ስሜት የሚደረግ "ከልብ የመነጨ ጸሎት ነው"

ጨካኙ ዳኛ እንዲርፈድላት ያደረገችው ያች መበለት እንዴት እንዲፈርድላት እንዳደረችገው አታያትም? ( ሉቃ 18፥3) አንተ ግን ሩኅሩኅና መሐሪ የኾነ ጌታ ነው ያለህ። እርሷ በጠላቶቿ ላይ እንዲፈርድላት ነው የጠየቀችው፤ አንተ ግን እምትጠይቀው ስለራስህ ድኅነት ነው።

፬• አራተኛ መንገድ አለ እርሱም "ምጽትዋ ነው " ይህም እጅግ በጣም ታላቅ የኾነ ኃጢአትን የሚስተርይ ኃይል አለውና።

ናቡከደነጾር ኃጢትን ንቅስ ጥቅስ አርድጎ ወደ ክኅደት ሁሉ በገባ ጊዜ እንድህ ብሎታልና፦ "ንጉስ ሆይ ! ምክሬ ደስ ያሰኝህ ኃጢአትህም ለጽድቅ በደልህን ለድኾች በመመጽወት አስቀር" (ዳ.ን 3፥27 ) ይህ ቸርነትና ሰውን መውደድስ ምንስ ይስተካከለዋል? እንዴት ያልከኝ እንደሆነ ስፍር ቁጥር የሌለውን ኃጢአት ከሰራ በኋላ ከዚያ ኹሉ በደል በኋላ እንደርሱ ለሆኑ ሰወች ርኅራኄን ቢያደርግ ከተገዳደረውና ከተጣላው አምላክ ጋር መታረቅ እንደሚችል ቃል ተገብቶለታልና ።

፭• አምስተኛው መንገድ "እንዲሁም ትሕትናና እራስን ማዋረድ ኃጢአትን ያደክማል"

ይህንንም ቀራጩ ያረጋግጥልናል አይኖቹን ወደ ሰማይ ለማንሳት እንኳንስ እስኪፈራ ድረስ በታላቅ ትሕትና ራሱን ባዶ ባደረገ ጊዜ "ጻድቅ ሆኖ ሄደ ተብሏልና ።(ሉቃ 18፥13) ስለዚህም ምንም ምግባር ቢኖርህም እንኳን በደልህን ከመናር በቀር በጎ ምግባርህን አታስበው። ያን ጊዜ እግዚአብሔር የበደል ሸምክህን ያራግፍልሃል።

ስለዚህ እነዚህን መንገደኞች ተመላለስባቸው እንጅ ሰነፍ አትኹን ።

("አምስቱ የንስሐ መንገዶች እና ሌሎች በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ" መጽሐፍ በ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የቀረበ)
“ማር ኤፍሬም ሶርያዊ”
የመንፈስ ቅዱስ ዕንዚራ (ܟܢܪܐ ܕܪܘܚܐ, Kenārâ d-Rûḥâ)፤የኤፍራጥስ ወንዝ፣ የኤዴሳ ዲያቆን (Deacon of Edessa)፤ የሶርያዎች ፀሓይ (the Sun of the Syrians)፤ የቤተ ክርስቲያን ምሰሶ (a Pillar of the Church) ተብሏል። ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ በግእዝ “ማር ኤፍሬም ሶርያዊ” በማለት ኢትዮጵያውያን ይጠሩታል፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም ይኽነን ሊቅ ሲያወድሰው፡-
“ሰላም ለኤፍሬም ደራሲ ዘጽሩይ ልሳኑ፤
አብያተ ክርስቲያናት ይሠረጉ በድርሳኑ”፡፡
(በድርሳኑ አብያተ ክርስቲያናት የሚሸለሙ (የሚያጌጡ) አንደበቱ የጠራ ለደራሲው ለኤፍሬም ሰላምታ ይገባል) ብሎታል፡፡

ማር ኤፍሬም ሶርያዊ ሕይወጡን እና ሥራዎቹን ያጠኑ አለማቀፍ ሊቃውንት እንደሚገልጹት ከሆነ በአጠቃላይ ከ14,000 በላይ ድርሳናትን እንደደረሰ ይታመናል፤ በግእዝ ከተተረጐሙት መጻሕፍት ውዳሴ ማርያምን ጨምሮ በጥንታዊ ብራና መጻሕፍቶቻችን ውስጥ ከ95 በላይ የቅዱስ ኤፍሬም መጻሕፍቶች ሲገኙ እጅግ በጣም ጥቂቶቹ ብቻ በሃይማኖተ አበው ላይና በግብረ ሕማማት ላይ ብቻ ለሕትመት ሲበቁ ሌሎቹ ግን በዘረፋ ብራናዎቹ ከሀገር በመውጣታቸው ምክንያት ሊገኙ አልቻሉም፡፡

የአምላክ እናትም ለርሷ ያለውን ጥልቅ ፍቅር አይታ ከልጇ አማልዳው “አኀዝ እግዚኦ መዋግደ ጸጋከ” (አቤቱ የጸጋኽን ማዕበል ግታልኝ) እስኪል ድረስ እጅግ በርካቶች መጻሕፍትን እንዲጽፍ ኾኗል፡፡ ለዚኽ ፍጹም አባትም ቅድስት ድንግል ማርያም ለሰባት ተከታታይ ቀናት በታላቅ ክብር ኾና እየተገለጸችለት ውዳሴዋን ሰተት አድርጋ አስደርሳዋለች፤ በዚኽም የአምላክ እናት “የቅዱስ ኤፍሬም እመቤት” ተብላ ትወደሳለች፡፡
=========================
ብራና ሚዲያ BRANA MEDIA
https://t.me/brana_Book
~~~~~
መ/ር ሚኪያስ ዳንኤል
*ተጻፈ ፪/፲፪/፳፻፲፬ ዓ.ም*
Mikiyas danail የፌስቡክ ፔጅ https://www.facebook.com/Mikiyas-danail-102145778357310/
+++++++++++++++++++
መልካም ንባብና ምርምር ይሁንለዎ
ማን ነው ወዳጄ! ስለ ጻድቁ ክብር ሲል የመግቢያ ትኬት የሚገዛኝ?
#ቡሄ_ሔ
የደብረ ታቦር በዓል ከዘጠኙ ዐበይት በዓላት አንዱ ቢሆንም በምዕመናን ዘንድ ቡሄ/ሔ በመባል ይታወቅል ለመሆኑ የደብረ ታቦር በዓል ለምን ቡሄ/ሔ እያልን እንጠራዋለን? ስለምንስ ችቦ እናበራለን? የሚጮኸው የጅራፍ ድምጽ ምንድነው ምሥጢሩ የሚለውን በአጭሩ እንመከታለን፡፡
=================_//_==============
ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ስለ ደብረ ታቦር በዓል አከባበር በኢትዮጵያ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ “ቡሄ/ሔ ዘውእቱ በዓለ ኖሎት ደቀ መዛሙርት “ ይህውም ደብረ ታቦር ወይም የቡሄ/ሔ በዓል የደቀ መዛሙርትና የእረኞች በዓል ነው እንደ ማለት ፡፡ ምክንያቱም በጥንቷ ኢትዩጵያ የደብረ ታቦርን በዓል እረኞች የቆሎ ተማሪዎች በስፋት ስለሚያከብሩት ነው፡፡
===============_//_=================
#ቡሄ፡- ማለት “የበራ የደመቀ የጐላ ብርሃን“ የብርሃን በዓል እንደ ማለት ነው ይህም በቅዱስ ወንጌል እንደተጻፈው ጌታችን በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን በገለጠ ጊዜ ፊቱ እንደ ፀሐይ በማብራቱ፥ ልብሱም አጣቢ በምድር ላይ ሊያነጣው እስከማይችል ድረስ በጣም ነጭ አንጸባራቂ በመሆኑ ነው ማቴ 17፥2 ማር9፥3 ሉቃ9፥29
=============_//_===================
#ቡሔ፡- ማለት ደግሞ “ደስታ ፍሥሐ“ማለት ይሆናል፡፡ ይህውም በትንቢት እንደተፃፈው ታቦር ወአርምንዔም በስመ ዘአከ ይትፈሥሑ መዝ88፥12 በዚህ ትንቢታዊ ቃል መሠረት በወቅቱ የጌታ ብርሃን በዙሪያቸው አብርቷል ከታቦርም እስከ አርምንዔም ተራራ ድረስ ታይቷል፡፡ ይህም መለኮታዊ ብርሃን በወረደበት ጊዜ ከብቶቻቸውን ይጠብቁ የነበሩ በታቦርና በአርሞንየም አካባቢ ያሉ መዓልቱ የሌሊቱን ቦታ ስለ ወሰደው በሁኔታው ሐሴትን አድርገዋል፡፡ሙልሙል/ኀብስቱ፡- በታቦር ተራራ ዙሪያ ለነበሩት እረኛች ወላጆቻቸው ምግባቸውን ይዘው መሄዳቸውን ያጠይቃል፡፡ አንድም የኀብስቱ ምሳሌነት ለክርስቶስ ነው “አነ ውእቱ ኅብስተ ሕይወት ዘወረደ እምሰማያት” ዮሐ 6፥32-59
=================_//=================
#ጅራፍ፡- በደብረ ታቦር ዋዜማ ከፍ ያለ ቦታ ላይ ሆነን ጅራፍ የምናጮኸው መሠታዊ ሃይማኖታዊ ምሥጢር ምሳሌነት አለው።
++++++++++++++++++++++++++++++++++++
እግዚአብሔር አብ በመልክ የሚመስለኝ በባህሪ የሚተካከለኝን ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው አንድያ ልጄ ነው፡፡ እርሱን ስሙት ተቀበሉት ብሎ ድምጹን በደመና በደብረ ታቦር ተራራ ላይ የመሰከረበትን እያሰብን ነው፡፡
++++++++++++++++++++++++++++++++++++
የጅራፍ ጩኸት ከጫፍ ጫፍ ይሰማል በመዝሙረ ዳዊት “……….. ድምጻቸው ወደ ምድር ሁሉ ቃላቸውም አስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ፡፡” መዝ18፥4 በማለት የሐዋርያት ስብከት በዓለም ዳርቻ መድረሱን ያመለክታል፡፡ መኃ 2፥12
ሌላው የጅራፍ ጩኸት ማስደንገጡ ደግሞ ሦስቱ አዕማድ ጴጥሮስ፣ ያዕቆብና ዮሐንስ ድምጸ መለከትን ሰምተው ደንግጠው መውደቃቸውን ያስታውሳል፡፡
++++++++++++++++++++++++++++++++++++
በተጨማሪም የልጆቹ ወላጆች በታቦር ተራራ ዙሪያ የነበሩትን ልጆቻቸው ለመፈለግ ችቦ እያበሩ ሲሄዱ ልጆቹም ጅራፍ በማጮኽ ያሉበትን ሥፍራ መጠቆማቸውን ያስረዳል፡፡
ችቦ፡- ተሰብስበን ችቦ የማብራታችን ምሳሌ ደግሞ ጌታችን በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን የገለፀበት ምሳሌ በመሆኑ ነው፡፡ የሐ 8፥1፣ መዝ 26፥1 “እግዚአብሔር ብርሃኔና መድሐኒቴ ነው……..”
================_//=================
#ማጠቃለያ፡- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የደብረ ታቦርን በዓል በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን ታከብረዋለች፤ ይኸውም በዕለቱ በዓሉን የሚያዘክር በቤተክርስቲያን ምንባባት ይነበባል፡፡ ቅዳሴ ይቀደሳል፣ ምስባክ ይሰበካል፣ ቃለ እግዚአብሔር ይሰጣል፣ ወረብ ይወረባል………… ወዘተ በዚህም ዕለት የቤ/ክ አባቶችና ምእመናን በዓሉን በደማቅ ሥነ ሥርዓት ያከብሩታል፤ ምክንያቱም ከላይ በስፋት እንደ ተመለከትነው ደብረ ታቦር እሥራኤላውያን የድል ካባ የደረቡበት መሳ 4፥1—3 የትርጓሜ ትምህርት የተሰጠበት ማቴ 15፥15፣ ኑፋቄ (ጥርጥር) የተወገደበት ማቴ 16፥13—20፣ ምሥጢረ ሥላሴን የተረዳንበት፣ የክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት የተሰበከበት፣ የሐዋርያት ባለሟልነት የተገለጠበት፣ የተግባር ትምህርት የተሰጠበት፣ አሉባልታና ተራ ወሬ የከሸፈበት፣ የቅዱሳን ነቢያት ሐዋርያት ክብር የተገለጠበት፣ የተቀደሰን ቦታ አክብሮት፣የተማርንበት የታየበት፣ ብሔረ ሕያዋን መኖሩ የተመሠከረበት፣ የትንሣኤ ሙታን ዋስትና የተረጋገጠበት ነው፡፡
++++++++++++++++++++++++++++++++++++
“በዘመኑም ፍጻሜ የእግዚአብሔር ቤት ተራራ በተራሮች ራስ ላይ ጸንቶ ይቆማል…………” ኢሳ ፪፥፪
••MIKIYAS DANAIL••
https://t.me/mikiyasBRANAbook
https://www.facebook.com/mikiyas.danail
=============//================
መልካም የደብረ ታቦር በዓል
••••••••••••••
©መ/ር ሚኪያስ ዳንኤል
ነሐሴ12/2014
የማይቀርበት ጉባኤ
የማይቀርበት ጉባኤ
በሥጦታ ወር የተሳተፋችሁበትን (ገቢ ያደረጋችሁበትን) ወረቀተ(bank sleep) ፖስት አድርጉልን።
እናመሰግናለን!