በክርስቶስ ( in christ)
690 subscribers
98 photos
34 videos
41 files
37 links
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Download Telegram
አልተካህም - Hawaz Tegegn
ተወዳጁ የደስታዬ እልልታ
.        አልተካህም
 ዲ/ን ሐዋዝ ተገኝ - Live
@yedestaye_elilta
@yedestaye_elilta
           △Join Us
( ቁስልን በቁስል )


ሀኪምን እና ህመምተኛ ያገናኛቸው ዋና አላማ ፈውስ ነው ። ህመምተኛው አንዳች ለፈውስ የሚሆን መድሃኒት እየናፈቀ ከሀኪም ዘንድ አብዝቶ ይመላለሳል። ምን ያስደስተሃል ቢባል ካለብኝ ደዌ ፈፅሞ መፈወስ በማለት መልስ ይሰጣል ።

ከሰው ልጅ በላይ ደዌ ያደቀቀ ከወዴት ይገኛል???  በጥቅልሉ ሰው ታሟል !! ሀጢያት እያሳደደው ቁስሉን ይመዘምዝበታል፤ ህመሙን ያበዛበታል  ። ከሁሉ የሚበልጠው ደግሞ በሀጢያት ከመውደቃችን  የተነሳ ከተፈጠርንበት አላማ ማለትም ከእግዚአብሔር ጋር ካለን ህብረት መለየታችን ይብሱን ያማል አዎን ከአምላክ ህልውና መጉደል እንዴት ያም ይሁን ?? እንጃ😭 !!!

መታከም አስፈለገን !! ያውም የማያዳግም ህክምና ግድ አለን ። ቁስላችን የሚያክ ሳይሆን ከስር መሰረቱ ነቅሎ የሚጥል ፍቱን የሆነ ህክምና አሰኝቶናል ። ምን መሰኘት ብቻ እውነትም ለእኛ እውነተኛ የሆነ ሰማያዊ ህክምና በምድር ላለን ለእኛ ተገኝቷል ። ህክምናው በእጅጉ ከአይምሮ በላይ ነው ። ሀኪሙ ...ኢየሱስ ፣ መድሃኒቱ..ኢየሱስ ፣ ፈዋሹ ...ኢየሱስ ፣ ቁስለኛው...ኢየሱስ ...ወይ ጉድ እንዴት ያለ ህክምና ይሆን ??😭

ቁስላችንን በቁስሉ አሻረው በሚፈሰው ክቡር ደሙ ቁስላችን ታጠበ ፣ በቁስሉ የቁስላችንን ህመም ወሰደ (የህማም ሰው ተባለ) ፣ ቁስሉ  ምንም ጠባሳ የማያስቀር መድሃኒት ሆነን  ፣ በቁስሉ ውስጥ አይዞአችሁ ወዳችኋለው አለን።  ጴጥሮስ ይሆን አይቶ እኮ ነው በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ ያለው ። ከእግዚአብሔር ጋር የለያየን ያንን ክፉ በሽታ ፣ደዌ ፣ ህመም ማለትም የሀጢያት በሽታ በመገረፉ ቁስሉ ፣ በመስቀል ላይ የመዋረድ ጥግ ህመም  ቁስላችን ወሰደው ፣ የሀጢያት አበሳችን ነቀለው ወደ እግዚአብሔር ወደ ልጁም ህብረት ሳበን ፣ ጠራን ። አሜን የሚያድን ፣ የሚፈውስ፣ ወደ ህይወት የሚጣራ ቁስል የጌታ የኢየሱስ ቁስል ብቻ ነው ።

ጌታ ኢየሱስ ቁስለኛው ፈዋሽ ፣ ህመምተኛው ሀኪም ፣ ቁስለኛው መድሃኒት ነው ።ቁስላችን በቁስሉ አሻረው ።



ፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
( የህዝቡ አንበሳ )


 
 እግዚአብሔር ህዝብ አለው ። በስሙ የተጠራለት ፣ለእርሱ የሚወግን ፣ ለመንግስቱ የሚያደላ ፣ ከእርሱ ለእርሱ የሆነ ህዝብ አለው !!

ይሔ ህዝብ ከየትኛው ወገን በተለየ መልኩ የሚመላለስበት እሴት ይለየዋል ።እነዚህ እሴቶች ሰማያዊ መልክ ያላቸው መንፈሳዊ እውነት ያዘሉ መርህ ናቸው ። እነዚህም :- ፍቅር ፣ ተስፋ ፣እምነት ናቸው ። በእነዚህ እሴቶች ይሔ ህዝብ ወደ ላይ ከአምላኩ ጋር በእምነት ይወዳጃል ፣ ወደጉን እርስ በእርሳቸው አልፎም ከሌሎች ወገኖች ጋር በፍቅር ይዘረጋል ፣ በእምነት እና በፍቅር የጨበጣቸውን እውነቶች በተስፋ ይኖራል ። እንዴት የታደለ ህዝብ ይሁን ??


የህዝቡ ታሪክ ቢታይ በዚህ አለም ኑሮ እንደምናውቃቸው የሃገረ መንግስት ግንባታ በታላላቅ አብዮቶች የጎለመሰ ወገን አይደለም ። አለማችን ላይ በአብዮት ያልተቀጣጠለ ፣ ያልተቀጠለ የህዝብ ክፍል አለ ለማለት ያዳግታል ። ይሔ ህዝብ ግን ያለ አንዳች የሰዎች አመፅ ፣ የሁኔታዎች ጋጋታ የቆመ ህዝብ ነው ። የኋሊት ተጉዘን የእግዚአብሔር ህዝብ ታሪክ ብንቃኝ ጎልቶ የሚታየው መነሻው ጎልጎታ ነው እርሱም የጎልጎታው ገድል ነው ።   አንዴ የተደረገ ነገር ግን ዘላለማዊ የሆነ ገድል በእነርሱ ላይ ይውለበለባል ። ጀግናዋ ደግሞ በቀራንኒዮ ላይ እርቃኑ ፣ ተዋርዶ የተሰቀለው መሲህ(ክርስቶስ) ነው። በዚህ ህዝብ ከእርሱ ከተሰቀለው ውጪ አንዳች ጉዳይ የላቸው ነጋ ጠባ ፣ መሸ ሄደ የሚደጋገመው ፣ የማያረጀው ህያው ዜና ይሔው ነው ። የተሰቀለው በዚህ ህዝብ ዘንድ አይሰለችም ፣ አይቀልም እንደ እንደዘበት አይታይም መስቀሉ ደግሞ ምልክታቸው ብቻ ሳይሆን ህይወታቸውም ጭምር ነው ። በህይወታቸው ተሸክመውት ይዞራሉ መስቀሉን በመሸከም ጀግናቸው ይመስላሉ ።

ምንስ ሲሆን ጀግናቸው ሆነ  ??
ዘመን በሌለው እሱነቱ ዘመን ኖረው፣  በማይወሰነው እሱነቱ በስጋ ተወስኖ ፣ በማይዋረደው ክብሩ ስለ ሰው ተዋርደ ፣ የአርያምን ርቀትን እንደቁብ ሳይቆጥር ጨክኖ መጣ ፣ የአባቱን እቅፍ ሊተረክ በሌሎች እቅፍ ስር ብቅ አለ ።  ከእርሱ በቅር ማን ጀግና ሊኖር ይሁን ??ለንግስና አይዋደቅም ሁሉ በእጁ  ነው ። ዙፋን አያጓጓውም ለሌሎች ብቻ እየቃተተ ለመሞት የመስቀልን ጉዞ ይጓዛል ። ወትሮም በእየ አደባባዪ ፣ በእየ ምስባኳ፣ በእየ ክብረ በአሏ እሱ በደመቀ ልብ ታሳዋለች ። የህዝቡ አንበሳ እንደ በግ ለእርድ የተሰቃየው መሲሁ ኢየሱስ ነው ።

የህዝቡ ታሪክ ከተሰቀለው መሲህ ላይ ይመሰረታል ። በደም የተሰራ ፣ በክርስቶስ ሞት እና ትንሳኤ ድንኳኑን የጣለ ህዝብ ነው ። ይሔም ህዝብ የእግዚአብሔር ህዝብ (ቤተክርስቲያን ) በክርስቶስ ኢየሱስ አምነው ወደ እግዚአብሔር መንግስት የተጨመሩ ፣ ወደ ፍቅሩ የፈለሱ ፣ሰማያዊ ወገኖች ፣ የንጉስ ካህናት ፣ የጌታ ቅዱሳን ናቸው ።



ፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
መዳፉ ላይ ቁስል ካያችሁ #የህመም ሰው ካስተዋላችሁ #ውዴ እርሱ ነው #ነፍሴን የያዛት #በእንቁ ሳይሆን በደም የገዛት 😭


🎼
@ownkin
@cgfsd
ድካሜን በተረዳሁ ቁጥር በራሴ መፍጨርጨር አቆማለሁ ፀጋው ለመደገፍ  አብዝቼ ወደ ፀጋው ዙፋን እቀርባለሁ !!

(እፉፉ በፀጋ ከራስ መገላገል እንዴት ያለ እፎይታ ነው)


@ownkin
@cgfsd
( ይርባል እንዴ ??)

ሁለት ወዳጆች ጨዋታቸው ይጫወታሉ ። አንድኛዋ ለተወሰነ አመታት እስራኤል ኑሯለች ። ስለ እስራኤል የምታወቀውን ለሌላኛዋ ጓደኛዋ ትነግራታለች ።
   " እስቲ ተይኝ አሁን አሜሪካ ፣ አውስትራሊያ ሀገር ነው ምናምንቴዎች ፤ ሀገር ማለት እስራኤል ነው ። መሬቱን እንደው ብታይ አሸዋ ነው ግን በልምላሜ አረጓዴ ነው። ለካ እውነት  ነው ... በመፀሀፍ ቅዱስ ማር እና ወተት የምታፈሰው የተባለላት ያለ አንዳች አይደለም ። አይምሮአቸውስ ብትይ የተባረከ በእውቀት የተሞሉ ናቸው ።

እንደው በየቤተክርስቲያኑ ምስባክ እንደው ስለጌታችን ታሪክ  ሲወራ በአይምሮዬ ኮለለል እያለ ይታየኛል  የጎበኘሁት ሁሉ  ።
  ጌታችን የተቀበረበት መቃብር ብትይ ፣ ክብሩ ከደቀመዛሙርቱ ጋር የተገለጠበት ደብረ ታቦር ፣ ሊሰቀል ሲል ቀድሞ የፀለየበት ጌተሰማኒ፣ አርባ ቀን አርባ ሌሊት ከፀለየ በኋላ ድንጋዩን ዳቦ አርግ ተብሎ የተፈተነበት ፣የተሰቀለበት ቀራኒዬ ጎልጎታ፣ ደግሞ በምፅአቱ ይመጣበታል የሚባለውንን ተራራ፣ ይሔ ይገርምሻ ስሙ ማን ነበር ??? ይሔ አራጣ ያበድር የነበረው አዎ አዎ አጭሩ ዘኪዬስ እሱ የወጣበት ዛፍ ሁላ ሳትቀር ነው ያየሁት ።
     ሌላኛዋ ጓደኛው በተራዋ ወይ ያንን ማየት የሚችል እንደው የተባረከ ነው!! አለች ፤ በረጅም እየተነፈሰች  እንባ ከአቀረሩ አይኖቿ ጋር ።
  ግን አንድ ጥያቄ ልጠቅሽ ....ግን እዛ ይርብሻል እንዴ?? (ይርባል እንዴ) ??   ማለት በቃ ይሔን እያየሽ አይርብሽም አይደል  ነፍስማ መቼም ይሔ አይታ ትጠግባለች እንጂ አትራብም ።
   የእስራኤሏ ሴትዬ አንገቷን ዝቅ አድርጋ ትዝታ እንደገረፈው ተክዛ አዎ ያጠግባል ብላ ቋጨችው።
.............................

.... ታዲያ እንዴት እንጥገብ??መቼም መንፈሳዊ ነገር ለመጥገብ የግድ ኢየሱሰስ የተወለደበት፣ እና የሞተበትን ብቻ ማየት አይጠበቅብንም ። እርሱ ራሱ የህይወት እንጀራ ነኝ ብሎናል እሱን ከበላን አይርበንም ማንነቱ ጥጋብ ሆኖናል።   

  ጋሽ ሰለሞን አበበ ገብረመድህን በአንድ የፅሀፉ ልጠፋቸው ላይ እንዲህ አሉ
  " መስቀል ላይ የተጋገረ እንጀራ "።
ግሩም አባባል እንደሆነ ተረድቻለሁ ። እግዚአብሔር መቼ የነፍስ ጠኔያችን እና ጉስቁላችን ለማከም፣ለማስታገስ፣ ለማጥገብ ብሎም ለማርካት አንድያውን በዘላለማዊ ፍቅሩ ህይወት እንዲሆንል ጋገረልን ። ከዛም የተጋገረውን በፍቅር ድምፅ ብሉልኝ አለ ። ከዚህ በላይ ምን የሚያጠግብ ህይወት አለ??ምንም !!
   የተጋገረውን እንጀራ እያሰብኩ አጭር ስንኝ ቋጠርኩ
        መስቀል ባሉት ምጣድ
                 ርሃብ ታሰረ
          የህይወት እንጀራው
                  መናው ተጋገረ

ለማስታወስ ያክል እግዚአብሔር እስራኤላዊያን በግብፅ ሳሉ ስለ ፋሲካው በግ በተመለከተ ከአዘዛቸው ትዕዛዝ አንዱ የፋሲካው በግ እንዲበሉ በመጀመሪያ ጥጋብ እንዲሆናቸው ነበር ።ግልፅ ያለ የኢየሱስ ምሳሌ ነው  ፋሲካችን ክርስቶስ ከሆነ ዘንዳ ምን እንበላለን ??ምንም !! እስራኤላዊያን ከግብፅ ወጥቸው ወደ ከነአን ለሚያደርጉት ጉዞ የበሉት የፋሲካ በግ ስንቅ ሆኖቸው ነው ። እኛስ የጀመርነው እውነተኛው መንፈሳዊ ህይወት ኢየሱስን ተመግበን አይደል ። የጀመርነውን ህይወት በድል የሚያስጨርሰን ሚስጥሩ የበላነው እውነተኛው መብል ኢየሱስ ነው ። እግዚአብሔር እንደዚህ የሚል አይመስላችሁም ..ብሉልኝ ይሔው ቢበሉት የማያልቅ ይሔው የሚትረፍረፍ ማዕድ ከሰማይ የሆነ የህይወት እንጀራ ። አባቶች መና በልተው ተራቡ በዛው በምድረበዳ ቀሩ ..እውነተኛ የህይወት እንጀራው ኢየሱስ የበላ ግን የዘላለም ህይወት ይቀናጃል ። ቲሞቲ ከለር የተባሉ ሰው እንዲህ አሉ " ኢየሱስ የህይወት እንጀራ ነኝ ሲል እግዚአብሔር ጋግሮላችኋል እያለ ነው "።

ጌታችን ኢየሱስ እሱ ራሱ የህይወት እንጀራ እንደሆነ ለተከተሉት ሊያሳውቅ በማሰብ 2አሳ እና 5እንጀራን አበዛላቸው ደስም አላቸው በሉ ተነጋገሩ መብዛቱ በራሱ አስደሳችነው አለማለቁም ሌላ አጃይብ ነው ።ግን ከበዛው ምግብ በላይ እሱ ኢየሱስ በእነርሱ ህይወት ሊበዛላቸው የህይወት እንጀራ ሊሆንላቸው እንደመጣ አልተገነዘቡም ነበር ።  2አሳ እና 5 እንጀራው በአንድ ጊዜ ተበልቷል ያው እዛ ቦታ ለነበሩት የህይወት እንጀራ ሁኖ ከመስቀል ላይ የተበላለው ግን ዛሬም ፣ነገም
  የሚበላ ለሁሉም የሚደርስ የተትረፈረፈ ማዕድ ነው ።


    በቀራንዬ ላይ ለእኛ በጉ ታርዷል
    ፈርኦን አይደለም ዲያቢሎስ ተረቷል
    በትረ ሙሴያችንም የጌታ መስቀል ነው
     በእሱ ቀጥቅጠን ነው ሞትን የገደልነው
                  (ዘማሪ ቴዎድሮስ)


ፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
አብዝቶ በመስቀሉ ስራ የተመሰጠ(የተደነቀ) በመዳኑ ውስጥ ያለውን ደስታ ያጣጥማል ።

@ownkin
@cgfsd
የመስቀሉን ሊሻን አርገን #የደሙን ሀብል አጥልቀን #በቀዩ ምንጣፍ ላይ በእምነት #ተራምደን ገብተናል ገነት #ድል ነስቶ ድል አልብሶናል #ኢየሱስ ማዕረግ ሁኖናል ።



🎼
@cgfsd
@ownkin
በመዳፍህ መሃል ያሳለፍከኝ #ጌታ ተቸንክረህ ደምተህ ሰው ያረከኝ #ጌታ የቱ ትከሻዬ ፍቅርህን ይችላል ከምገልፀው በላይ #ውለታህ ከብዶኛል ።


🎼
@ownkin
@cgfsd
የሰማይ ድባብ የቤዛነቱ ድባብ ነው ። ለዚህም ነው በሰማይ ታርደሃል እና እየተባለ ቅኔ የሚቀኙለት እዛም ሰማይ የቤዛነቱ ጠረን ይሸታል ፣ የቤዛነቱ መአዛ ያውዳል። ቤተክርስቲያንም የክርስቶስ የቤዛነት ድባብ ጉባኤዋን ያጥናል ፣ በመካከሏ የቤዛነቱ ደስታ ያስተጋባል፣ ቤዛነቱ ያንሰፈስፋታል፣ ቤዛነቱ ቀልቧን ይሰርቃል።


@ownkin
@cgfsd
#የዘላለም ርዕስ #የማያልቅ ምዕራፍ #የማይፈፀም ታሪክ #የማይጨረስ መፀሀፍ #የእሱ መች አልቆብን ሌላ እንጀምራለን #የተሰቀለውን ስንሰብክ እንኖራለን #ዋናው ኢየሱስ ነው  #ዋናው ክርስቶስ ነው #ከሞት ለተቤዥን #በደሙ መፍሰስ #በደሙ መፍሰስ #መቼ አወጅነው እና #የእርሱን ድንቅ ስራ


🎼
@ownkin
@cgfsd
(የነካኝ ምስክርነት)


በክርስቲያን ቤተሰብ በማደጌ ኢየሱስን የማውቀው ልክ  በመስቀል ላይ የተሰቀለ  የሚል ብቻ እውቀት ነበር ። በኋላ ግን ከዛ ያለፈ እንደሆነ አስገራሚ ማንነት እንዳለው ስረዳ አብዝቼ አብዝቼ ኢየሱስ የሚለው ስም አንስቼ ማንነቱ አስቤ አልጠግብ አልኩ ።ስለ ኢየሱስ ሳይሆን ራሱን ኢየሱስ ማወቅ ጀመርኩ ።

ኢየሱስ አስገራሚ ማንነት አለው 😍



@ownkin
@cgfsd
ውዳችን ኢየሱስ ወከባ አያስቆመውም .... ለአየር መተንፈስ በሚከብደው  በግፊያ መሀል ግን ለነካው ይቆማል ።
             
      ምስክር : የደሟ ምንጭ የቆመላት


@ownkin
  @cgfsd
#ኢየሱስ -በምድር በነበረበት ዘመን አለመኖሬ ኢየሱስ እንዲያመልጠኝ አላደረገኝም....በምድር አይኑር እንጂ እሱ ወዳለበት መንፈስ ቅዱስ አድርሶኛል......እርሱ ካልገለጠልን በቀር ኢየሱስን ማወቅም መንካትም አንችልም 😇😘

Ariel

@ownkin
@cgfsd
ኢየሱስ ከክህደት በኋላ የምትሾም አንተ ነህ !! የወደድካቸውን እስከ መጨረሻው የምትወድ ወዳጅ
(የግንዱ ላይ ሰንባች)



  ኢየሱስ ገበሬው አባቴ ነው በማለት ሊሰራ ስላለው ታላቅ ስራ የአንበሳውን ድረሻ የአባቱ  እንደሆነ አስገንዝቦናል ። በእርግጥም እግዚአብሔር ጥንቅቅ ያለ ገበሬ ነው ። ገበሬ ያነገበው አላማውን እስከ መጨረሻው እንጥፍጣፊ ደረጃ ድረስ ሰንቆ የሚተጋ ነው። ሁሉም ነገር የሚታየው ከግቡ የተነሳ ነው ቢጥል ፣ቢያነሳ፣ ቢቆፍር፣ ቢቧጥጥ የሰነቃትን ተልዕኮ ለማሳካት እንጂ እግረ መንገድ የሆነ ራዕይ የለውም ። በጠዋት ማልዶ ሲነሳ ፀሀይ በምስራቅ በኩል መፈንጠቋ ለእሱ ቅንጦት አይደለም ምርቱን በላቀ ሁኔታ ለመጨመር ሌላ እድል አድርጎ ያየዋል ። ዝናብ ደግሞ እንዲሁ አየር ንብረቱ እየሞቀው ስለረበሸው እንደው ቀዝቀዝ ለማለት አይሻውም ይልቁንም የዘራቸው ዘሮቹ እንዲያቆጠቁጡ ተስፋ ይጥልበታል ። ሀብቱም ፣ ንብረቱም ፣ ጉልበቱም  የሚያፈሰው (ኢንቭስት የሚያደርገው ) መሬቱ ላይ ነው ። ምናልባት በለስ ካልቀናችው ደግሞ ኪሳራውም በእጅጉ አስደንጋጭ ነው የሚሆነው ያለውን በሙሉ የሰጠው ለዚሁ ጉዳይ ነውና ።  የእግዚአብሔር ገበሬነት ግን በእጁጉ ይለያል ብሎም ይማርካል ።  ቆይ ግን እግዚአብሔር ምን ገዶት ገበሬ ሆነ 🤔???

    ህብረት ...ህብረት ...ህብረት ብቻ ነው ። እግዚአብሔር የገበሬን ግብር ይዞ የተጠራው እኛን ሆን ብሎ ለማስገረም አይደለም ህብረት ፈልጎ እንጂ ። አምላካች ህብረት የሚወድ ህብረት የሚያረግ አምላክ ነው ። ለዚህም ነው ገበሬ ብሎ የተጠራው !!  የፈለገው ህብረት ደግሞ በግንድ በቅርንጫፍ በኩል የሆነ ህብረት ነው ።  የሚያስገረም ነው ነገር ቢኖር ገበሬው እግዚአብሔር ለዚህ ህብረት ኢንቭስት ያደረገው ዋጋ ነው ። ኢንቭት ለማድረግ ውሃ አልቋጠረም ፣ አፈር አልጫረም ፣አቧራ አላስነሳም አንድ ልጁ ላይ ጨከነበት ። የተጠቀመው ውሃ የልጁን ደም ፣ የተኮኮተው መሬት የልጁን ስጋ ነበር ። ወደር የማይገኝለት ዘላለማዊ ልጁን ስለ ሌሎች ተብሎ ተማገደ ። እግዚአብሔር የመጨረሻ ኢንቭትመንቱን በልጁ ቤዛነት (ምትክነት ) በኩል አደረገው ።ገበሬው አምላካችን በልጁ በኩል አለምን የሚያርስበት ቀን በጉጉት ለቀደሙት አባቶች አመላከተ ። ዘመቻ ቀራኒዮ ...ዘመቻ ጎልጎታ የኢንቭትመንቱ የመጨረሻ ግብ ነበር ። ምንም እንኳን እንደ ገጠሩ አካባቢዎች ለአጨዳ ቀን ሆ ብሎ ሰው በሆታ ሊሰበስብ አልመጣ ይብሱኑ በአንድነት በጩኸት ስቀለው ስቀለው እያሉ አንድያውን አሳልፎ በሰጠው የገበሬውን ልጅ ላይ ለመግፋት ተሰበሰቡ እንጂ ።  ገበሬው በኩራት ይሔው ኢንቭትመንቴ ይሔው ከመስቀሉ ላይ ፣ ይሔው የተሰቀለው እሱ ላይ የሚበቅሉ ቅርጫፎች ውጤቶቼ ናቸው ።ቅርጫፎቹ የሚያፈሩት ፍሬው ደግሞ የሰራውት ታላቅ የኢንቭትመንት ስራ ማሳያዎች ናቸው ።

የልጁ ደም ከልጁ እና ከገበሬው አባቱ ጋር ህብረት ማድረጊያ ነው ።ህብረቱ  ከተሰቀለው ጋር አብሮ መሰቀል ነው ፣ ህብረቱ ከሞተልን ጋር መሞት ነው ፣ ህብረቱ ከተነሳልን ጋር መነሳት ነው ፣ህብረቱ ለግንዱ መኖር፣ ህብረቱን ግንዱ ለመምሰል መኖር ፣  ህብረቱ ገበሬው በቅርጫፉ በኩል የገለጠልን ፍቅር መቋደስ፣ መተንፈስ ፣ ለሌሎች ማካፍል ፣ በፍቅሩ መፈንደቅ ፣ በፍቅሩ መኩራራት ይሔ ህብረቱ ነው ... ገበሬው ... እኛ ለግንዱ ሰጥቷል ... በግንዱ በኩል የማያስፈልገው አኑሮሯል ። ግንዱ ሁል ጊዜ እንዲህ ይለናል በእኔ ኑሩ !! በእኔ ቆዩ ፣ በእኔ ሰንብቱ ፣ በእኔ ክረሙ ፣ በፍቅሬ ኑሩ እያለ ከእርሱ ጋር ወዳለው ቁርኝት እና መጣበቅ ይጠራናል ።

በግንዱ ክርስቶስ ጋር መቆየት ምርጫ የሌለው የህይወት ስርአታችን ነው ። ከእርሱ ጋር እንድንከርም ተጠርተናል ። የገበሬውን የልብ ትርታ ለመረዳት ካሰነበተን ግንድ ጋር መሰንበት ነው ። ግንድ ለቅርጫፎቹ የሚሆኑትን ሚኒራል ፣ ውሃ የሚያስፈልጉት ሁሉ ወደ ቅርጫፎቹ ሳያጓድል ያደርሳል የእኛም ግንድ ክርስቶስ ለእኛ የሚያስፈልገን ለህብረቱ የሚጠቅመን ማንነቶች ሳያዛንፍ ይሰጠናል ።


ከግንዱ ክርስቶስ ጋር ስለተወዳጀን ነው ፤ የገበሬውን ቤተሰብ የተቀላቀል ነው።
በክርስቶስ ( ግንዱ) እና በእኛ (በቅርንጫፎቹ) መካከል ያለው የወዳጅነት መጣበቅ ምክኒያቱ ክርስቶስ ላይ እንድንቆይ የወደደው ገበሬ ነው ።


ፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
ክርስቶስ በቅዱሳት መጻሕፍት በኹሉም ስፍራ አለ! ለዚህ ነው መጽሐፍ ቅዱስን አብዝቼ የምወድደው!

Diakon abenezer

@cgfsd
@ownkin