በክርስቶስ ( in christ)
699 subscribers
98 photos
34 videos
41 files
37 links
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Download Telegram
ወልድ ተዛመደ ህዝቡን ተጠጋጋ
ገንዘቡ አደረገ  የሰውን ልጅ ስጋ

@ownkin
@cgfsd
ፍንትው አለ  አየነው ያየንን
የፅድቅ ፀሃዩ ኢየሱስ ወጥቶልን

@cgfsd
@ownkin
“የጸጋው ጅረት በትሕትና ዝቅ ወዳለ እንጂ ወደ ዕቡይ ልብ ሽቅብ አይወጣም።”
ቅዱስ በርናርድ
መልኬን በመልክህ ላይ ቀራንዮ አይቼ
እንዴት ዝም ልበል ፍቅርህን ጠጥቼ


🎼
@cgfsd
@ownkin
ግድ የለም ስለ ብዙ ነገር አይግባን እግዚአብሔር በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል የሰራልን ስራ ግን በቅጡ እንረዳ ።

@ownkin
@cgfsd
Forwarded from Meareg Taye
filye.aac
27 MB
"ቤተ ክርስቲያን ቴአትር ቤት፣ እኛም ኮሜዲያን ሆነናል!"

ብዙ አማኝ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚመጣው ለመዝናናት ነው። ሌላውም ሰው ጆክ ሲያምረው፣ መሳቅ ሲፈልግ የእኛን ቪዲዮዎች ነው የሚያየው። በኢየሱስ ስም፣ በልሳን፣ በጸሎት ከት ከት ብሎ ይስቃል። እኛም አብረን እንስቃለን። ምንም ስለማይመስለን ቪዲዮውን እየተቀባበልን እንስቃለን። የእግዚአብሔር ስም መቀለጃ ስለሆነ የሚያየው አይፈራው፣ የሚሰማን አይፈራው። እኛም አላከበድነው በሚገባ አላሳየነው፣ አልገለጥነው፣ አላመጣነው...።

የአብዛኞቻችን አገልጋዮች ዓላማ ራሱ ሰውን ማዝናናት ነው፤ "ምን ብናገር አዝናናዋለሁ ነው።" የብዙ ምዕመናን የቤተ ክርስቲያን፣ የስብከትና የአገልግሎት ምርጫ "የት ብሄድ ያልተካበደ ነገር እሰማለሁ"፣ "መዝናናት አገኛለሁ" የሚል ነው። ቤተ ክርስቲያን ቴአትር ቤት፣ እኛም ኮሜዲያን ሆነናል።

ተዉ እንጂ ብዙም ሩቅ ባልሆኑ ዓመታት፣ የዛሬ ሰልሳ ዓመት ወደ ኃላ "ሪዋይንድ" ብታደርጉ አማኞች የሚፈራ ምገስ ነበራቸው። ሰዎቹ ዛሬም በሕይወት ስላሉ ሄዳችሁ ጠይቋቸው። በቤተ ክርስቲያናቸው ደጃፍ ማለፍ እንኳ ያስፈራ ነበር። ሕይወታቸው ግርማ ነበረው። መልዕክታቸው አስደንጋጭ ነበር። ለማስደንገጥ ብለው ሳይሆን እግዚአብሔር በመካከላቸው ነበር።

እዚያ ለመቀለድ አትሄድም፤ ንሰሐ እንጂ ጆክ ትዝ አይልህም። አጋንንት ይወጣል፣ ሰዎች ይፈወሳሉ። የእግዚአብሔር ቃል፣ የክርስቶስ ወንጌል ይሰበካል። ይኼ ሁሉ የሚሆነው ፐርፌክት [ፍጹማን] ክርስቲያኖች ስለሆኑ አይደለም። ግን የኢየሱስን ስም አስከባሪዎች ነበሩ።

አሁን ቢያንስ ስሙ በሆነ መንገድ ይከበር ዘንድ ብንጸልይስ? ቢያስፈልግ ኮሜዲያኖቹን በጊዜ ቢወስደን፤ ይኼም እኮ አንዱ መንገድ ነው። ወይም ደግሞ ጥግ አስይዞን የሆኑ ሌሎች ሰዎች ቢያመጣ፣ እኛ ዕድሉን አልጠቀም ስላልን ሌላን ትውልድ ቢያስነሳልን፣ ስላላየናቸው እንጂ እግዚአብሔር ስሙን የሚያስከብሩለት ልጆች አሉታ!...

በዚህ ዘመን ወንጌል የምንሰብክበት ብዙ መድረክ አግኝተን፣ ሚዲያ ተመቻችቶልን አልተጠቀምንበትም። በየሰዉ ቤት የጌታን ስም ተሸክመን ለመግባት እንደዚህ ዘመን ዕድል ተሰጥቶን ያውቃል እንዴ? እኛ ግን ጆካችንን ይዘን ገባንበት፤ እግዚአብሔርን መሳለቂያ አደረግነው። ስለዚህ ወገኖቼ በአሕዛብ መካከል የተነቀፈው ማንነቱ የቀለለው ስሙ መልሶ እንዲከብድ በየትኛውም መንገድ ምክንያት ለመሆን መጸለይ አለብን።

ዶ/ር ማሙሻ ፈንታ
አዲስ ኪዳን የአሮጌውን ኪዳን እንኳን የበለጠ እንድንረዳ የሚያደርገን መክፈቻ ቁልፍ ነው ።

(የክርስቶስ ትንሳኤ ገፅ 43)

@ownkin
@cgfsd
የእግዚአብሔር ልጅ ክፍል አንድ
<unknown>
ይሔ ድንቅ መፀሃፍ ነው በትረካ ብትሰሙት ታተርፋላችሁ ። ኢየሱስን በተመለከተ አስደናቂ ስራ ነው ። የኢየሱስ ማንነት ለፈለገ እጅግ ግሩም መፀሀፍት ነው ።

@cgfsd
ያበጃጁኝ እጆችህ እንዴት የተዋቡ ናቸው
የደሙልኝ እጆችህ እኔንም ያቀፉ ናቸው
ዛሬም መተህ በኔ ላይ ጌታ ሆይ ጫናቸው😭


🎼😍

@cgfsd
@ownkin
ኢየሱስን መውደድ የአንድ ጊዜ ውሳኔ ወይም ስሜት አይደለም።

ኢየሱስን መውደድ በየቀኑ በየሰዓቱ በየደቂቃው የምመርጠው ምርጫ ነው።

ለኢየሱስ ፍቅሬን ምገልጥለት እና ማሳየው በእያንዳንዱ ቀን እና ጉዳይ ላይ በምወስነው ውሳኔ ነው።

ለምንድንነው የእግዚአብሔርን ፈቃድ ፍላጎት ብቻ ምታደርገው?
*ኢየሱስን ስለምወደው!!

ለምንድነው የራስህን ፈቃድ እና ፍላጎት ማታደርገው?
*ኢየሱስን ስለምወደው!!

ለምንድነው ለአባትህ ደስታ እና ሳቅ እንደዚህ ምትጨነቀው?
*ኢየሱስን ስለምወደው!!

ለምንድነው ደስ እንዳለህ ማትኖረው?
*ኢየሱስን ስለምወደው!!

ስለምወደው    ስለምወደው
ጌታ ኢየሱስን ስለምወደው

ለክርስቲያን ለምን ተብሎ ሲጠየቅ እጅግ ውብ የሆነ ምክንያቱ "የወደደኝን ኢየሱስ ስለምወደው ነው" ነው።


* ኢየሱስን ስለምወደው
Audio
የሰው ልጅ የሚያመጣው ፅድቅ የመርገም ጨርቅ ነው ።እግዚአብሔር ያመጣው ፅድቅ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ።


@cgfsd
@ownkin
Forwarded from HUFELLOW
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ውድ የፌሎአችን ልጆች እንዴት ናቹ?

🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉

እነሆ አዲስ ነገር ይዘንላችሁ መጥተናል በፌሎአችን ኳየር የተዘጋጀ ስምህ የሚል  ርዕስ ያለው የመዝሙር clip በቅርብ ቀን ይዘን እንቀርባለን!!! Stay tuned

Excited!! 💯
ስምህ | Hufellow choir new Gospel music video

View - Like - share

@HUfellow

#share_to_others
ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ
ምግበ ስጋ ወምግበ ነፍስ

🎼

@ownkin
@cgfsd
ጌታ ኢየሱስ ደግመህ ደጋግመህ ነፍሴን በቤዛነትህ ጠረን እጠናት 😭!!

@ownkin
@cgfsd
አድራሻው እና ማንነቱ በክርስቶስ ሆኖ የተደላደለ ሰው የሚኖርበት የኑሮ መርህ የህይወት መንፈስ ህግ ይባላል እሱ መንፈስ ቅዱስ ነው ።   (ሮሜ 8:2)

@ownkin.
@cgfsd
ክርስቶስ የተጠማ ሁሉ ከእርሱ እንዲጠጣ እግዚአብሔር በዚህ ምድረ-በዳ ዓለም ያፈለቀው ምንጭ እንጂ የ 66 መጽሐፍ ጭምቅ ሐሳብ ብቻ ወይም እጣሬ አይደለም።
Christ is not a commentary.

Ylu

@cgfsd
@ownkin