Forwarded from Amanuel Gezahgne
Telikoachin magazine v - 7 Final.pdf
2 MB
Forwarded from ruth Fikadu
YouTube
Song of the week ኢየሱስን የሚያውቀው ማነው
እየሱስን የሚያውቀው ማን ነው? እኔ /2/
እየሱስን የሚያውቀው ማን ነው? እኔ /2/
በስእል አይደለም ያልኩት ያወቀው ማነው?
በወሬም አይደለም ያልኩት ያወቀው ማነው?
እየሱስን የሚያውቀው ማን ነው? እኔ /2/
ተመራምሮ አይደለም ያልኩት
ያወቀው ማነው? በሩቁም አይደለም ያልኩት ያወቀው ማነው?
እየሱስን የሚያውቀው ማን ነው? እኔ /2/
በቃሉ /2/ ከሆነ የምታውቀውከኔ ጋር አድንቀው
በቃሉ…
እየሱስን የሚያውቀው ማን ነው? እኔ /2/
በስእል አይደለም ያልኩት ያወቀው ማነው?
በወሬም አይደለም ያልኩት ያወቀው ማነው?
እየሱስን የሚያውቀው ማን ነው? እኔ /2/
ተመራምሮ አይደለም ያልኩት
ያወቀው ማነው? በሩቁም አይደለም ያልኩት ያወቀው ማነው?
እየሱስን የሚያውቀው ማን ነው? እኔ /2/
በቃሉ /2/ ከሆነ የምታውቀውከኔ ጋር አድንቀው
በቃሉ…
(የግንዱ ላይ ሰንባች)
ኢየሱስ ገበሬው አባቴ ነው በማለት ሊሰራ ስላለው ታላቅ ስራ የአንበሳውን ድረሻ የአባቱ እንደሆነ አስገንዝቦናል ። በእርግጥም እግዚአብሔር ጥንቅቅ ያለ ገበሬ ነው ። ገበሬ ያነገበው አላማውን እስከ መጨረሻው እንጥፍጣፊ ደረጃ ድረስ ሰንቆ የሚተጋ ነው። ሁሉም ነገር የሚታየው ከግቡ የተነሳ ነው ቢጥል ፣ቢያነሳ፣ ቢቆፍር፣ ቢቧጥጥ የሰነቃትን ተልዕኮ ለማሳካት እንጂ እግረ መንገድ የሆነ ራዕይ የለውም ። በጠዋት ማልዶ ሲነሳ ፀሀይ በምስራቅ በኩል መፈንጠቋ ለእሱ ቅንጦት አይደለም ምርቱን በላቀ ሁኔታ ለመጨመር ሌላ እድል አድርጎ ያየዋል ። ዝናብ ደግሞ እንዲሁ አየር ንብረቱ እየሞቀው ስለረበሸው እንደው ቀዝቀዝ ለማለት አይሻውም ይልቁንም የዘራቸው ዘሮቹ እንዲያቆጠቁጡ ተስፋ ይጥልበታል ። ሀብቱም ፣ ንብረቱም ፣ ጉልበቱም የሚያፈሰው (ኢንቭስት የሚያደርገው ) መሬቱ ላይ ነው ። ምናልባት በለስ ካልቀናችው ደግሞ ኪሳራውም በእጅጉ አስደንጋጭ ነው የሚሆነው ያለውን በሙሉ የሰጠው ለዚሁ ጉዳይ ነውና ። የእግዚአብሔር ገበሬነት ግን በእጁጉ ይለያል ብሎም ይማርካል ። ቆይ ግን እግዚአብሔር ምን ገዶት ገበሬ ሆነ 🤔???
ህብረት ...ህብረት ...ህብረት ብቻ ነው ። እግዚአብሔር የገበሬን ግብር ይዞ የተጠራው እኛን ሆን ብሎ ለማስገረም አይደለም ህብረት ፈልጎ እንጂ ። አምላካች ህብረት የሚወድ ህብረት የሚያረግ አምላክ ነው ። ለዚህም ነው ገበሬ ብሎ የተጠራው !! የፈለገው ህብረት ደግሞ በግንድ በቅርንጫፍ በኩል የሆነ ህብረት ነው ። የሚያስገረም ነው ነገር ቢኖር ገበሬው እግዚአብሔር ለዚህ ህብረት ኢንቭስት ያደረገው ዋጋ ነው ። ኢንቭት ለማድረግ ውሃ አልቋጠረም ፣ አፈር አልጫረም ፣አቧራ አላስነሳም አንድ ልጁ ላይ ጨከነበት ። የተጠቀመው ውሃ የልጁን ደም ፣ የተኮኮተው መሬት የልጁን ስጋ ነበር ። ወደር የማይገኝለት ዘላለማዊ ልጁን ስለ ሌሎች ተብሎ ተማገደ ። እግዚአብሔር የመጨረሻ ኢንቭትመንቱን በልጁ ቤዛነት (ምትክነት ) በኩል አደረገው ።ገበሬው አምላካችን በልጁ በኩል አለምን የሚያርስበት ቀን በጉጉት ለቀደሙት አባቶች አመላከተ ። ዘመቻ ቀራኒዮ ...ዘመቻ ጎልጎታ የኢንቭትመንቱ የመጨረሻ ግብ ነበር ። ምንም እንኳን እንደ ገጠሩ አካባቢዎች ለአጨዳ ቀን ሆ ብሎ ሰው በሆታ ሊሰበስብ አልመጣ ይብሱኑ በአንድነት በጩኸት ስቀለው ስቀለው እያሉ አንድያውን አሳልፎ በሰጠው የገበሬውን ልጅ ላይ ለመግፋት ተሰበሰቡ እንጂ ። ገበሬው በኩራት ይሔው ኢንቭትመንቴ ይሔው ከመስቀሉ ላይ ፣ ይሔው የተሰቀለው እሱ ላይ የሚበቅሉ ቅርጫፎች ውጤቶቼ ናቸው ።ቅርጫፎቹ የሚያፈሩት ፍሬው ደግሞ የሰራውት ታላቅ የኢንቭትመንት ስራ ማሳያዎች ናቸው ።
የልጁ ደም ከልጁ እና ከገበሬው አባቱ ጋር ህብረት ማድረጊያ ነው ።ህብረቱ ከተሰቀለው ጋር አብሮ መሰቀል ነው ፣ ህብረቱ ከሞተልን ጋር መሞት ነው ፣ ህብረቱ ከተነሳልን ጋር መነሳት ነው ፣ህብረቱ ለግንዱ መኖር፣ ህብረቱን ግንዱ ለመምሰል መኖር ፣ ህብረቱ ገበሬው በቅርጫፉ በኩል የገለጠልን ፍቅር መቋደስ፣ መተንፈስ ፣ ለሌሎች ማካፍል ፣ በፍቅሩ መፈንደቅ ፣ በፍቅሩ መኩራራት ይሔ ህብረቱ ነው ... ገበሬው ... እኛ ለግንዱ ሰጥቷል ... በግንዱ በኩል የማያስፈልገው አኑሮሯል ። ግንዱ ሁል ጊዜ እንዲህ ይለናል በእኔ ኑሩ !! በእኔ ቆዩ ፣ በእኔ ሰንብቱ ፣ በእኔ ክረሙ ፣ በፍቅሬ ኑሩ እያለ ከእርሱ ጋር ወዳለው ቁርኝት እና መጣበቅ ይጠራናል ።
በግንዱ ክርስቶስ ጋር መቆየት ምርጫ የሌለው የህይወት ስርአታችን ነው ። ከእርሱ ጋር እንድንከርም ተጠርተናል ። የገበሬውን የልብ ትርታ ለመረዳት ካሰነበተን ግንድ ጋር መሰንበት ነው ። ግንድ ለቅርጫፎቹ የሚሆኑትን ሚኒራል ፣ ውሃ የሚያስፈልጉት ሁሉ ወደ ቅርጫፎቹ ሳያጓድል ያደርሳል የእኛም ግንድ ክርስቶስ ለእኛ የሚያስፈልገን ለህብረቱ የሚጠቅመን ማንነቶች ሳያዛንፍ ይሰጠናል ።
ከግንዱ ክርስቶስ ጋር ስለተወዳጀን ነው ፤ የገበሬውን ቤተሰብ የተቀላቀል ነው።
በክርስቶስ ( ግንዱ) እና በእኛ (በቅርንጫፎቹ) መካከል ያለው የወዳጅነት መጣበቅ ምክኒያቱ ክርስቶስ ላይ እንድንቆይ የወደደው ገበሬ ነው ።
✍ ፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
ኢየሱስ ገበሬው አባቴ ነው በማለት ሊሰራ ስላለው ታላቅ ስራ የአንበሳውን ድረሻ የአባቱ እንደሆነ አስገንዝቦናል ። በእርግጥም እግዚአብሔር ጥንቅቅ ያለ ገበሬ ነው ። ገበሬ ያነገበው አላማውን እስከ መጨረሻው እንጥፍጣፊ ደረጃ ድረስ ሰንቆ የሚተጋ ነው። ሁሉም ነገር የሚታየው ከግቡ የተነሳ ነው ቢጥል ፣ቢያነሳ፣ ቢቆፍር፣ ቢቧጥጥ የሰነቃትን ተልዕኮ ለማሳካት እንጂ እግረ መንገድ የሆነ ራዕይ የለውም ። በጠዋት ማልዶ ሲነሳ ፀሀይ በምስራቅ በኩል መፈንጠቋ ለእሱ ቅንጦት አይደለም ምርቱን በላቀ ሁኔታ ለመጨመር ሌላ እድል አድርጎ ያየዋል ። ዝናብ ደግሞ እንዲሁ አየር ንብረቱ እየሞቀው ስለረበሸው እንደው ቀዝቀዝ ለማለት አይሻውም ይልቁንም የዘራቸው ዘሮቹ እንዲያቆጠቁጡ ተስፋ ይጥልበታል ። ሀብቱም ፣ ንብረቱም ፣ ጉልበቱም የሚያፈሰው (ኢንቭስት የሚያደርገው ) መሬቱ ላይ ነው ። ምናልባት በለስ ካልቀናችው ደግሞ ኪሳራውም በእጅጉ አስደንጋጭ ነው የሚሆነው ያለውን በሙሉ የሰጠው ለዚሁ ጉዳይ ነውና ። የእግዚአብሔር ገበሬነት ግን በእጁጉ ይለያል ብሎም ይማርካል ። ቆይ ግን እግዚአብሔር ምን ገዶት ገበሬ ሆነ 🤔???
ህብረት ...ህብረት ...ህብረት ብቻ ነው ። እግዚአብሔር የገበሬን ግብር ይዞ የተጠራው እኛን ሆን ብሎ ለማስገረም አይደለም ህብረት ፈልጎ እንጂ ። አምላካች ህብረት የሚወድ ህብረት የሚያረግ አምላክ ነው ። ለዚህም ነው ገበሬ ብሎ የተጠራው !! የፈለገው ህብረት ደግሞ በግንድ በቅርንጫፍ በኩል የሆነ ህብረት ነው ። የሚያስገረም ነው ነገር ቢኖር ገበሬው እግዚአብሔር ለዚህ ህብረት ኢንቭስት ያደረገው ዋጋ ነው ። ኢንቭት ለማድረግ ውሃ አልቋጠረም ፣ አፈር አልጫረም ፣አቧራ አላስነሳም አንድ ልጁ ላይ ጨከነበት ። የተጠቀመው ውሃ የልጁን ደም ፣ የተኮኮተው መሬት የልጁን ስጋ ነበር ። ወደር የማይገኝለት ዘላለማዊ ልጁን ስለ ሌሎች ተብሎ ተማገደ ። እግዚአብሔር የመጨረሻ ኢንቭትመንቱን በልጁ ቤዛነት (ምትክነት ) በኩል አደረገው ።ገበሬው አምላካችን በልጁ በኩል አለምን የሚያርስበት ቀን በጉጉት ለቀደሙት አባቶች አመላከተ ። ዘመቻ ቀራኒዮ ...ዘመቻ ጎልጎታ የኢንቭትመንቱ የመጨረሻ ግብ ነበር ። ምንም እንኳን እንደ ገጠሩ አካባቢዎች ለአጨዳ ቀን ሆ ብሎ ሰው በሆታ ሊሰበስብ አልመጣ ይብሱኑ በአንድነት በጩኸት ስቀለው ስቀለው እያሉ አንድያውን አሳልፎ በሰጠው የገበሬውን ልጅ ላይ ለመግፋት ተሰበሰቡ እንጂ ። ገበሬው በኩራት ይሔው ኢንቭትመንቴ ይሔው ከመስቀሉ ላይ ፣ ይሔው የተሰቀለው እሱ ላይ የሚበቅሉ ቅርጫፎች ውጤቶቼ ናቸው ።ቅርጫፎቹ የሚያፈሩት ፍሬው ደግሞ የሰራውት ታላቅ የኢንቭትመንት ስራ ማሳያዎች ናቸው ።
የልጁ ደም ከልጁ እና ከገበሬው አባቱ ጋር ህብረት ማድረጊያ ነው ።ህብረቱ ከተሰቀለው ጋር አብሮ መሰቀል ነው ፣ ህብረቱ ከሞተልን ጋር መሞት ነው ፣ ህብረቱ ከተነሳልን ጋር መነሳት ነው ፣ህብረቱ ለግንዱ መኖር፣ ህብረቱን ግንዱ ለመምሰል መኖር ፣ ህብረቱ ገበሬው በቅርጫፉ በኩል የገለጠልን ፍቅር መቋደስ፣ መተንፈስ ፣ ለሌሎች ማካፍል ፣ በፍቅሩ መፈንደቅ ፣ በፍቅሩ መኩራራት ይሔ ህብረቱ ነው ... ገበሬው ... እኛ ለግንዱ ሰጥቷል ... በግንዱ በኩል የማያስፈልገው አኑሮሯል ። ግንዱ ሁል ጊዜ እንዲህ ይለናል በእኔ ኑሩ !! በእኔ ቆዩ ፣ በእኔ ሰንብቱ ፣ በእኔ ክረሙ ፣ በፍቅሬ ኑሩ እያለ ከእርሱ ጋር ወዳለው ቁርኝት እና መጣበቅ ይጠራናል ።
በግንዱ ክርስቶስ ጋር መቆየት ምርጫ የሌለው የህይወት ስርአታችን ነው ። ከእርሱ ጋር እንድንከርም ተጠርተናል ። የገበሬውን የልብ ትርታ ለመረዳት ካሰነበተን ግንድ ጋር መሰንበት ነው ። ግንድ ለቅርጫፎቹ የሚሆኑትን ሚኒራል ፣ ውሃ የሚያስፈልጉት ሁሉ ወደ ቅርጫፎቹ ሳያጓድል ያደርሳል የእኛም ግንድ ክርስቶስ ለእኛ የሚያስፈልገን ለህብረቱ የሚጠቅመን ማንነቶች ሳያዛንፍ ይሰጠናል ።
ከግንዱ ክርስቶስ ጋር ስለተወዳጀን ነው ፤ የገበሬውን ቤተሰብ የተቀላቀል ነው።
በክርስቶስ ( ግንዱ) እና በእኛ (በቅርንጫፎቹ) መካከል ያለው የወዳጅነት መጣበቅ ምክኒያቱ ክርስቶስ ላይ እንድንቆይ የወደደው ገበሬ ነው ።
✍ ፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
(ኢየሱስ ያስቀናል )
የፈንሳዩ የጦር አበጋዝ ናፖሊዮ ቦናባርቴ በርከት ያሉ የውጊያ ድሎች አስመዝግቧል፣ ብዙዎች ማርኳል ነገር ግን ስለ ጌታ ኢየሱስ ማራኪነት ተደንቆ ያለ ጠብመንጃ ሚሊየኖች በፍቅር እንደሚከተሉት በአግራሞት ተናግሯል ። የክርስቶስ ማንነት በእጅጉ የሚገዛው በሰባአዊነቱ የሚጠቀሰው ማህተመ ጋንዲ የኢየሱስ ባህሪ ለዕድሜ ዘመኑ እንደጠቀመው ፣ ስብዕናው ውስጡ እንደሚገዛው አትቷል ።አለም በመዝገቧ ከትባ ያስቀመጠቻቸው ታላላቅ ሰዎች በናዝሬቱ ኢየሱስ የተነሳ እየተገረሙ ወቸው ጉድ በማለት እጃቸውን በአፋቸው አጣምረው ጭነዋል ። በአሜሪካን ለሰው ልጆች እኩልነት ወገቡን አስሮ በቀዳሚነት ዘብ የቆመው ማርቲን ሉተር ኪንግ እንዲህ ይላል "ኢየሱስ ለፍቅር ፣ ለእውነት ፣ ለመካምነት ፅንፈኛ ነበር " በማለት ሀሳቡን አጋርቷል ። በዘመነ አብርሆት ለአለም መንቃት አስተፆ የተጫወተው ፈላስፋው ሩሶ ደግሞ በበኩሉ "ሶቅራጥስ እንደ ፈላስፋ ሞተ ኢየሱስ ግን እንደ እግዚአብሔር ሞተ " በማለት እይታውን አስቀምጧል ።
የቀጠናው አስተዳዳሪ ሔሮዶስ እልፍ እየተከተሉት እንደሆነ በተአምራቱ እና በትምህርቱ አካባቢውን አልፎ ዙሪያ ገባውን የናዝሬቱ ኢየሱስ እንደሞላ ሲሰማ ስለ ስልጣኑ ስጋት ቢኖረው እሱን ሊሰማ ይናፍቅ ነበር ። መሲሁ ኢየሱስ ላይ ጥርስ የነከሱት የካህናት አለቆች ወታደር አሰማርተው ተጠፍንጎ እንዲመጣ ትዕዛዝ ቢሰጡም የተላኩት ወታደሮች ግን በማንነቱ ፣ በትምህርቱ እና በስራው ተመስጠው የተላኩበትን ረስተው ጆሮ ዳባ ልበስ በማለት ስለ ንፅህናው ሽንጣቸውን ገትረው ተከራክረዋል ። የሸንጎ አባሉ ፈሪሳዊው ኒቆዲሞስ ኢየሱስን ለማወቅ በሌሊት ያለበት ድረስ አነፍንፎ መቷል ። ኢየሱስ ያስቀናል !! እንስማህ፣ እንይህ፣ እንንካህ ፣እንከተልህ ያስብላል ።
በጨዋታችን መሃል አንድ የምቀርበው ወዳጄ በቤተክርስቲያን መሃል ስለተንሰራፋው ክርስቶስን ስለማይመስለው ልምምዳችን ሲያስብ እንዲህ ይለኛል " እኔ ግን አይገባኝም ክርስቶስን እንዲህ አለውቀውም ኧረ እኔ ኢየሱስ እንደዚህ አላውቀውም ..ይገርምሃል ኢየሱስ ክርስቶስን እንደግል አዳኝ አድርጌ የተቀበልኩት በመፀሀፍ ቅዱስ የዕለት ተለዕለት ጥናት ወቅት ነበር ። በተለይም ደግሞ የወንጌል መፀሀፍት ማቴዎስ ፣ ማርቆስ ፣ሉቃስ እና ዩሀንስ ወንጌላት ላይ ያነበብኩት ጌታ ባህሪው፣ ትህትናው ፣ ፍቅሩ ፣ አላማው ፣ ታዛዥነቱ ያስቀናኝ ነበር " በማለት አውግቶኛል ። በትክክል !! በተጨባጭ !!! ለዚህም ነው የዕውቀት ቀንዲሉ ሊቁ አልበርታን አንስታይል እንዲህ ያለው " ማንም የኢየሱስን እውነተኛነትን ሳይሰማ ወንጌልን ማንበብ አይችል " ያለው። ይሔው ነው !! የወንጌል መፀሀፍት ስናነብ የኢየሱስ የማንነት ውበት ይወረናል ፣ የባህሪው ማራኪነት ይማርከናል፣ አስደናቂነቱ ቀልባችንን ይገዛዋል ። የህይወት ታሪክ አይደለም አምላክ በስጋ የኖረው ህይወት እንጂ ። በቃ እንዲህ ነው የክርስትና ወጉ ኢየሱስን ከሰማበት ፣ካወቀበት ጊዜ ጀምሮ መመረቅ ለሌለው ጊዜ ዘወትር በውስጥ እየተቃጠሉ ፣ እጅ እየነሱ መኖር ።
ኢየሱስ ያስቀናል
✍ ፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
የፈንሳዩ የጦር አበጋዝ ናፖሊዮ ቦናባርቴ በርከት ያሉ የውጊያ ድሎች አስመዝግቧል፣ ብዙዎች ማርኳል ነገር ግን ስለ ጌታ ኢየሱስ ማራኪነት ተደንቆ ያለ ጠብመንጃ ሚሊየኖች በፍቅር እንደሚከተሉት በአግራሞት ተናግሯል ። የክርስቶስ ማንነት በእጅጉ የሚገዛው በሰባአዊነቱ የሚጠቀሰው ማህተመ ጋንዲ የኢየሱስ ባህሪ ለዕድሜ ዘመኑ እንደጠቀመው ፣ ስብዕናው ውስጡ እንደሚገዛው አትቷል ።አለም በመዝገቧ ከትባ ያስቀመጠቻቸው ታላላቅ ሰዎች በናዝሬቱ ኢየሱስ የተነሳ እየተገረሙ ወቸው ጉድ በማለት እጃቸውን በአፋቸው አጣምረው ጭነዋል ። በአሜሪካን ለሰው ልጆች እኩልነት ወገቡን አስሮ በቀዳሚነት ዘብ የቆመው ማርቲን ሉተር ኪንግ እንዲህ ይላል "ኢየሱስ ለፍቅር ፣ ለእውነት ፣ ለመካምነት ፅንፈኛ ነበር " በማለት ሀሳቡን አጋርቷል ። በዘመነ አብርሆት ለአለም መንቃት አስተፆ የተጫወተው ፈላስፋው ሩሶ ደግሞ በበኩሉ "ሶቅራጥስ እንደ ፈላስፋ ሞተ ኢየሱስ ግን እንደ እግዚአብሔር ሞተ " በማለት እይታውን አስቀምጧል ።
የቀጠናው አስተዳዳሪ ሔሮዶስ እልፍ እየተከተሉት እንደሆነ በተአምራቱ እና በትምህርቱ አካባቢውን አልፎ ዙሪያ ገባውን የናዝሬቱ ኢየሱስ እንደሞላ ሲሰማ ስለ ስልጣኑ ስጋት ቢኖረው እሱን ሊሰማ ይናፍቅ ነበር ። መሲሁ ኢየሱስ ላይ ጥርስ የነከሱት የካህናት አለቆች ወታደር አሰማርተው ተጠፍንጎ እንዲመጣ ትዕዛዝ ቢሰጡም የተላኩት ወታደሮች ግን በማንነቱ ፣ በትምህርቱ እና በስራው ተመስጠው የተላኩበትን ረስተው ጆሮ ዳባ ልበስ በማለት ስለ ንፅህናው ሽንጣቸውን ገትረው ተከራክረዋል ። የሸንጎ አባሉ ፈሪሳዊው ኒቆዲሞስ ኢየሱስን ለማወቅ በሌሊት ያለበት ድረስ አነፍንፎ መቷል ። ኢየሱስ ያስቀናል !! እንስማህ፣ እንይህ፣ እንንካህ ፣እንከተልህ ያስብላል ።
በጨዋታችን መሃል አንድ የምቀርበው ወዳጄ በቤተክርስቲያን መሃል ስለተንሰራፋው ክርስቶስን ስለማይመስለው ልምምዳችን ሲያስብ እንዲህ ይለኛል " እኔ ግን አይገባኝም ክርስቶስን እንዲህ አለውቀውም ኧረ እኔ ኢየሱስ እንደዚህ አላውቀውም ..ይገርምሃል ኢየሱስ ክርስቶስን እንደግል አዳኝ አድርጌ የተቀበልኩት በመፀሀፍ ቅዱስ የዕለት ተለዕለት ጥናት ወቅት ነበር ። በተለይም ደግሞ የወንጌል መፀሀፍት ማቴዎስ ፣ ማርቆስ ፣ሉቃስ እና ዩሀንስ ወንጌላት ላይ ያነበብኩት ጌታ ባህሪው፣ ትህትናው ፣ ፍቅሩ ፣ አላማው ፣ ታዛዥነቱ ያስቀናኝ ነበር " በማለት አውግቶኛል ። በትክክል !! በተጨባጭ !!! ለዚህም ነው የዕውቀት ቀንዲሉ ሊቁ አልበርታን አንስታይል እንዲህ ያለው " ማንም የኢየሱስን እውነተኛነትን ሳይሰማ ወንጌልን ማንበብ አይችል " ያለው። ይሔው ነው !! የወንጌል መፀሀፍት ስናነብ የኢየሱስ የማንነት ውበት ይወረናል ፣ የባህሪው ማራኪነት ይማርከናል፣ አስደናቂነቱ ቀልባችንን ይገዛዋል ። የህይወት ታሪክ አይደለም አምላክ በስጋ የኖረው ህይወት እንጂ ። በቃ እንዲህ ነው የክርስትና ወጉ ኢየሱስን ከሰማበት ፣ካወቀበት ጊዜ ጀምሮ መመረቅ ለሌለው ጊዜ ዘወትር በውስጥ እየተቃጠሉ ፣ እጅ እየነሱ መኖር ።
ኢየሱስ ያስቀናል
✍ ፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
(ጌታ ኢየሱስ )
የራሴ ድምፅ ብዙ ጊዜ ረበሽኝ ፣ እኔነቴ ያለ ቅጥ መፈናፋኛ አሳጣኝ ፣ ድካሜ ጉልበቴን ለግሞ ያዘኝ ፣ የምሰማው ነገር አስደነገጥ በዚህ ሁሉ ግን ስምህ መማፀኛ ግንብ ሆነኝ ። በዙሪያ ካሉት ሁሉ ዘልዮ አመለጥኩበት ። ቃላት አጥቼ ጌታ ኢየሱስ ጌታ ኢየሱስ እያለኩ ለማምለጥ ጠራሁት ነገር ግን ማምለጡን ረስቼ የጠራሁት ስምህ ጣፈጠኝ ጌታ ኢየሱስ ብዬ ሳልጨርስ ከእንደገና ስሙን መጥራት ናፈቀኝ ። ጌታ ኢየሱስ ስለው የተወጋው ጎኑ ትውስ ይላል፣ጌታ ኢየሱስ ስለው የፈሰሰው ደሙ እንደ ወንዝ ጅረት በአይነ ህሊናዬ እልፍ ይላል፣ ጌታ ኢየሱስ ስለው በመስቀል እንደ ተንጠለጠ ወድሃለው ሲለኝ ይሰማኛል ፣ ጌታ ኢየሱስ ስለው ልክ በሌለው ጭንቀቴ ውስጥ ልክ የሌለው ሰላሙ ይፈሳል፣ ጌታ ኢየሱስ ስለው ሀዘን ጥላውን ባጠላብኝ ነፍሴ ውስጥ ደስታው እንደ ማለዳ ፀሀይ ይፈነጥቅብኛል ፣ ጌታ ኢየሱስ ስለው በውስጤ ያለው ቅዱሱ መንፈስ ደግሜ እንድጠራው ጉልበት ይሆነኛል ።
ሰሞኑን ብዙ ተጨነኩ ፣ ብዙ አዘንኩ ፣ብዙ አነባሁ ፣ ብዙ ተልፈሰፈስኩ እና ብዙ ብዙ ልል አስቤ ልፀልይ ተንበረከኩ ጌታ ኢየሱስ ጌታ ኢየሱስ ብቻ ብዬ ስጣራ በአንድ ቃል ብዙ ተነፈስኩ ፣ አረፍኩ ፣ እፎይይ አልኩ !!
ጌታ ኢየሱስ😍
@ownkin
@cgfsd
የራሴ ድምፅ ብዙ ጊዜ ረበሽኝ ፣ እኔነቴ ያለ ቅጥ መፈናፋኛ አሳጣኝ ፣ ድካሜ ጉልበቴን ለግሞ ያዘኝ ፣ የምሰማው ነገር አስደነገጥ በዚህ ሁሉ ግን ስምህ መማፀኛ ግንብ ሆነኝ ። በዙሪያ ካሉት ሁሉ ዘልዮ አመለጥኩበት ። ቃላት አጥቼ ጌታ ኢየሱስ ጌታ ኢየሱስ እያለኩ ለማምለጥ ጠራሁት ነገር ግን ማምለጡን ረስቼ የጠራሁት ስምህ ጣፈጠኝ ጌታ ኢየሱስ ብዬ ሳልጨርስ ከእንደገና ስሙን መጥራት ናፈቀኝ ። ጌታ ኢየሱስ ስለው የተወጋው ጎኑ ትውስ ይላል፣ጌታ ኢየሱስ ስለው የፈሰሰው ደሙ እንደ ወንዝ ጅረት በአይነ ህሊናዬ እልፍ ይላል፣ ጌታ ኢየሱስ ስለው በመስቀል እንደ ተንጠለጠ ወድሃለው ሲለኝ ይሰማኛል ፣ ጌታ ኢየሱስ ስለው ልክ በሌለው ጭንቀቴ ውስጥ ልክ የሌለው ሰላሙ ይፈሳል፣ ጌታ ኢየሱስ ስለው ሀዘን ጥላውን ባጠላብኝ ነፍሴ ውስጥ ደስታው እንደ ማለዳ ፀሀይ ይፈነጥቅብኛል ፣ ጌታ ኢየሱስ ስለው በውስጤ ያለው ቅዱሱ መንፈስ ደግሜ እንድጠራው ጉልበት ይሆነኛል ።
ሰሞኑን ብዙ ተጨነኩ ፣ ብዙ አዘንኩ ፣ብዙ አነባሁ ፣ ብዙ ተልፈሰፈስኩ እና ብዙ ብዙ ልል አስቤ ልፀልይ ተንበረከኩ ጌታ ኢየሱስ ጌታ ኢየሱስ ብቻ ብዬ ስጣራ በአንድ ቃል ብዙ ተነፈስኩ ፣ አረፍኩ ፣ እፎይይ አልኩ !!
ጌታ ኢየሱስ😍
@ownkin
@cgfsd