ብራና ሚዲያ BRANA MEDIA
361 subscribers
1.3K photos
11 videos
146 files
169 links
Download Telegram
በሥጦታ ወር የተሳተፋችሁበትን (ገቢ ያደረጋችሁበትን) ወረቀተ(bank sleep) ፖስት አድርጉልን።
እናመሰግናለን!
†††_ርኅወተ ሰማይ_†††

`````

"እውነት እውነት እላችኋለሁ:: ሰማይ ሲከፈት: የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ::"
(ዮሐ. ፩፥፶፪)

• ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት: አራተኛው መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት: ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ዕለት ስለሆነች "ርኅወተ ሰማይ-ሰማይ የሚከፈትባት ቀን::" ትባላለች::

አሁን በሰማይ መዘጋት መከፈት ኑሮበት አይደለም:: የሰው ልጆችን ልመና ቅዱሳን መላእክት ያለ ከልካይ የሚያሳርጉበት: አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የጸሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለሆነ እንዲህ ተባለ እንጂ::

እመቤታችን ድንግል ማርያም ለአጼ ናዖድ እንደ ነገረቻቸው በዚህች ዕለት ሁሉም ቅዱሳን ስለሚታሰቡ: የእግዚአብሔር የምሕረት መዝገቡ ስለሚከፈት: ዕለቷን ክብርት ያሰኛታል:: በቅዱስ ሩፋኤል አበጋዝነት (መሪነት) በዚህች ዕለት ለዓመት የሚበቃ ምሕረት ይገኛል::

ስለዚህም አባቶቻችን በዚህች ሌሊት ሦስት መቶ ስልሳ አምስት አቡነ ዘበሰማያትን ሲጸልዩ ያድራሉ:: በሌላ ወገን ደግሞ የጌታ ዳግም ምጽዓቱ መታሰቢያ እንደ መሆኗ ትልቅ ትኩረትም ይሰጣታል::
ቸሩ ጌታችን ከተከፈተች ገነት ከተነጠፈች ዕረፍት ሁላችንንም ያድርሰን::

•ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት•

```````````````````````

"በሰው ቊስል ላይ የተሾመ ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ሩፋኤል ነው" ሄኖክ፮÷፫
ቅዱስ ሩፋኤል በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት በደረጃው ሦስተኛ ነው:: በመጀመሪያዋ ዕለተ ፍጥረት እግዚአብሔር መቶ ነገደ መላእክትን ፈጥሮ በአሥር ከተማ ሲያኖራቸው የቅዱስ ሩፋኤል ዕድል ፈንታው ራማ ሆነች::

በዚያም "መናብርት" ተብለው ለሚጠሩ አሥሩ ነገድ አለቃ (መሪ) ሆኖ በፈጣሪው ተሹሟል:: በኋላም "መጋብያን" በሚባሉ በሃያ ሦስቱ ነገድ ላይ ሹሞታል:: ይህች ዕለትም በዓለ ሲመቱ ናት::

አንድ ቀን ጌታችን ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ ሐዋርያቱ ቅዱስ ሩፋኤልን እንዲያስተዋውቃቸው ለመኑት:: ጌታም ሦስቱን ሊቃናት (ሚካኤል: ገብርኤል እና ሩፋኤል) ይመጡ ዘንድ አዘዛቸው::

ቀጥሎም ቅዱስ ሩፋኤልን "ክብርህን ንገራቸው::" አለው:: እርሱም ለጌታ ሰግዶ ለሐዋርያት ብዙ ምሥጢር ነገራቸው:: በተለይ ስሙን ለሚጠሩ: መታሰቢያውን ለሚያከብሩ የሚደረገውን ጸጋ አብራርቶላቸው ዐረገ::

በመጽሐፈ ጦቢት ላይ ተጽፎ እንደምናገኘው ቅዱሱ መልአክ ሰው (አዛርያን) መስሎ: ጦብያን ለትዳር አብቅቶ: ሣራን አስማንድዮስ ከሚባል ሰይጣን አድኖ: የጦቢትን ዓይን አብርቷል:: በገድላተ ቅዱሳን እንደምናየውም ለብዙ ቅዱሳን ረዳታቸው ሆኖ ገድላቸውን አስፈጽሟል::

ታሪክ እንደሚለው ይህች ቀን ለቅዱስ ሩፋኤል ቅዳሴ ቤቱም ናት:: በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በቅዱስ ቴዎፍሎስ ዘእስክንድርያ አማካኝነት ቤቱ ታንጿል:: የሚገርመው ደግሞ የታነጸው በዓሣ አንበሪ ጀርባ: ደሴት ላይ ነው:: በመልአኩ አጋዥነትም ለሦስት መቶ ዓመታት አገልግሏል::

ቅዱስ ሩፋኤል
• መራኄ ፍኖት (ጦቢያን መንገድ መርቷልና)
•መልአከ ከብካብ (የጦቢያና የሣራን ጋብቻ ስለባረከ
•መስተፍስሒ (ልቡናን ደስ የሚያሰኝ)
• አቃቤ ሥራይ (ባለ መድኃኒት ፈዋሽ)
• መዝገበ ጸሎት (የጸሎት መዝገብ መክፈቻ የተሰጠው)
• ሊቀ መናብርት (በዙፋን ላይ በክብር የሚቀመጡ መላእክት መሪ)
• ፈታሔ ማኅጸን (የሰውንም ሆነ የእንስሳትን ማኅጸን የሚፈታ)
• መወልድ (አዋላጅ: ምጥን የሚያቀል) ይባላል::
"ለሰብእ ወለእንስሳ ፈታሔ ማኅጸኖሙ አንተ" እንዲል::

“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” መዝሙር ፴፫፥፯

•ዳግም ምጽአት-የአለም ፍጻሜ•

``````````````````````

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስለ ዳግም ምጽአትና ስለ ዓለም መጨረሻ፣ ስለ ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታንም ሁልጊዜ የምታስተምር ቢሆንም በተለይ በዐቢይ ጾም ውስጥ ‹‹ደብረ ዘይት›› በሚለው ዕለተ ስንበትና በዓመቱ መጨረሻም በወርኃ ጳጉሜን ስለ ዳግም ምጽአትና ስለ ዓለሙ ፍጻሜ ከቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ነገረ ምጽአቱንና ምሥጢረትንሣኤ ሙታንን የሚመለከቱ ጥቅሶችን እያነበበችና ምእመናንን እያስጠነቀቀች በየጊዜው ትኵረት ሰጥታ ታስተምራለች። በእነዚህ ወቅቶች በቤተ ክርስቲያናችን የሚዘመረው መዝሙር፣ ቅዳሴውና ትምህርቱም ሁሉ ይህንኑ የተመለከተ ነው

"ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል።
አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም፤ እሳት በፊት ይቃጠላል፥ በዙሪያውም ብዙ ዐውሎ አለ።" መዝሙር ፵፱÷፪ ማቴ፳፬÷፩

•ቅዱስ መልከ ጼዴቅ•

```````````

ካህኑ መልከ ጼዴቅን ቅዱስ ጳውሎስ "የትውልድ ቁጥር የለውም: ለዘመኑም ጥንትና ፍጻሜ የለውም::" ይለዋል:: (ዕብ.7:3) ሐዋርያው ይህንን ያለው ለወልደ እግዚአብሔር ምሳሌ ሲያደርገው እንጂ ትውልዱ ከነገደ ካም ነው:: ወላጆቹም "ሚልኪ እና ሰሊማ" ይባላሉ::

ገና ከእናቱ ማኅጸን የተመረጠው ቅዱሱ "ካህነ ዓለም: ንጉሠ ሳሌም" ይባላል:: የዛሬ አምስት ሺ አምስት መቶ ዓመት አካባቢ ሴም ባኖረበት ቦታ (በደብረ ቀራንዮ) ለዘላለም ይኖራል:: ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከሰው ወገን እጅግ ክቡርም ነው::

•አፄ ዘርዓ ያዕቆብ

```````

ሃይማኖቱ የቀና ኢትዮጵያዊው ንጉሥ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ በኢትዮጵያ በነገሠባቸው ሠላሳ አራት ዓመታት (ከ1426 እስከ 1460 ዓ/ም) ብዙ በጐ ነገሮችን ሠርቷል:: ላለፉት ሰባ ዓመታት ግን አንዳንድ ጥቃቅን ሰብአዊ ስህተቶችን እየነቀሱ ተሐድሶዎቹ ስሙን ሲያጠፉት ኑረዋል::

ዛሬ ዛሬ ደግሞ የእኛ ቤት ሰዎችም ተቀላቅለዋቸዋል::
እነርሱ ያሉትን ይበሉ እንጂ ለእኛ ግን ዘርዓ ያዕቆብ ማለት:-
1.ጣዖት አምልኮን ከሃገራችን ለማጥፋት ብዙ ሺህ ካህናትን አሰልጥኖ አሰማርቷል::
2.የኑፋቄ ችግሮችን ለመቅረፍ ጉባኤያትን አዘጋጅቷል::
3.ከአሥራ አንድ ያላነሱ መጻሕፍትን በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት ደርሶ ለአገልግሎት አብቅቷል::
4.ብዙ መጻሕፍትን ከውጪ አስመጥቶ አስተርጉሟል (በተለይ ተአምረ ማርያምን)
5.ሰው ሁሉ ለእመ ብርሃንና ለመስቀሉ ፍቅር እንዲገዛ ጥረት አድርጓል
6.እመቤታችንን በፍጹም ልቡ ከመውደዱ የተነሳ ዛሬ ድረስ በሃገራችን ድንግል ማርያም "የዘርዓ ያዕቆብ እመቤት" እየተባለች ትጠራለች::
7.ብዙ አብያተ ክርስቲያናትን አንጾ: ብዙ ሥርዓቶችም በሊቃውንት እንዲሠሩ አድርጐ: ሌሎች ብዙ በጐ ተግባራትንም ፈጽሞ በዚህች ቀን ዐርፏል::
ቤተ ክርስቲያን ስለውለታቸው ዘርዓ ያዕቆብን: እናታቸው ጽዮን ሞገሳን እና አባታቸው ዳዊትን በክብር ታስባለች::

•ቅዱስ ሰራጵዮን ዘሰንዱን•

````````````````

ይህ ቅዱስ እጅግ የበዛ ሃብቱን ለነዳያን አካፍሎ: ወደ ሌላ ሃገር ሔዶ ለባርነት ተሽጧል:: በተሸጠበት ሃገርም በጸሎት ተግቶ ከክህደት ወደ ሃይማኖት መልሷቸዋል:: ክብሩን ሲያውቁበትም በተመሳሳይ ወደ ሌላ ሃገር ሒዶ አሕዛብን አድኗል:: በፍጻሜው ወደ በርሃ ገብቶ በተጋድሎ ኑሮ በዚህች ቀን ዐርፏል::

አምላከ ቅዱሳን የወዳጆቹን ሁሉ በረከትና ጸጋ ያብዛልን:: ለዓለምም ሰላሙን ይዘዝልን::
ጳጉሜን 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ርኅወተ ሰማይ (የሰማይ መከፈት)
2.ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት
3.ቅዱስ መልከ ጼዴቅ ካህን
4.አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ንጉሥ (የእመቤታችን ወዳጅ)
5.ቅዱስ ሰራጵዮን ዘሰንዱን
6.ቅዱስ አኖሬዎስ
7.ቅዱስ ቴዎፍሎስ
8.አባ ዮሐንስ
9.ቅዱስ ጦቢት
10.ቅዱሳን ጦብያና ሣራ

•መ/ር ሚኪያስ ዳንኤል•
•ጷግሜ 0፫/2014 ዓ/ም•
______†
ከበዓሉ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን።
~•••••••~•••••••~•••••~
“ስለ ሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን፤”
፩ኛ ዮሐንስ ፩፥፩!
••••••••••••••••••
የፌስቡክ ፔጃችንን ይቀላቀሉ ፤ ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, እና Share ያድርጉ :-
~•••••••~•••••••~•••••~
የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/mikiyas.danail

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063973695479

https://www.facebook.com/mikiyas24/

የቴሌግራም ቻናል : https://t.me/brana_Book
       †______†
ከበዓሉ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን።
              ~•••••••~•••••••~•••••~
“ስለ ሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን፤”
   ፩ኛ ዮሐንስ ፩፥፩!
                        ••••••••••••••••••
የፌስቡክ ፔጃችንን ይቀላቀሉ ፤ ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, እና Share ያድርጉ :-
                ~•••••••~•••••••~•••••~
የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/mikiyas.danail

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063973695479

https://www.facebook.com/mikiyas24/

የቴሌግራም ቻናል : https://t.me/brana_Book
†††[መስቀል ዓለም የዳነበት አምላካዊ ጥበብ ነው]†††
† ±±±±±±±±±±±±±±±±±±±±±±±±±±±±± †
መስቀል የሚለው ቃል ሲነገርም ሆነ ሲሰማ በክርስቲያኖች ልብ ውስጥ የመከራና የሰላም ስሜት በአንድ ላይ ይፈጥራል፡፡ ይህም በመከራ ውስጥ እንኳ ቢሆን እውነተኛ ሰላም ይገኝበታልና ነው፡፡ መስቀል ለድኅነተ ዓለም፤ ዓለምን ለማዳን ሲል የተሰቀለውን ክርስቶስን ያሳስበናል፡፡

መስቀል ዓለም የዳነበት አምላካዊ ጥበብ ነው:: ለዚህም ነው፤ አበው እግዚአብሔር አምላክ ይህንን ዓለም ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ ሰው ሆኖ በምድር ላይ ተመላልሶ፣ በመስቀል ተሰቅሎ፣ በሥጋው ሞቶ፣ ሞትን በትንሣኤው ድል ነሥቶ ዓለሙን ያዳነበት ጥበቡ ይበልጣል ያሉት፡፡ ይህን ዓለም ያዳነውም ንጹሓ ባሕርይ የሆነው አምላክ እንደ
ኃጢአተኛ ተቆጥሮ በመስቀል ተሰቅሎ ደሙን በማፍሰስ ስለሆነ መስቀል ይህ ዓለም ከደዌ ሥጋና ከደዌ ነፍስ የዳነበት የእግዚአብሔር ጥበብ ነው፡፡
★★መ/ር ሚኪያስ ዳንኤል★★
★መስከረም 14/2015 ዓ•ም★