በክርስቶስ ( in christ)
684 subscribers
96 photos
34 videos
41 files
36 links
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Download Telegram
ልመርቃችሁ ዝቅ በሉ...

ኢየሱስ ኢየሱስ እንዳላችሁ መሞት ይሁንላችሁ! እሱን ባከበራችሁት አፍ ስለእርሱ በተናገራችሁትና በዘመራችሁት አፍ ሌላን ነገር መዘባረቅ አይሁንላችሁ! ወደ እርሱ በሮጣችሁበት እግር ወደሌላው መገስገስ አይሁንላችሁ! ኢየሱስ ኢየሱስ ስትሉ ዘመናችሁ ይለቅ!
አሜን🙏😍
ቀና በሉ በቃ...!


Tsegaab-daniel

@ownkin
@cgfsd
ኢየሱስ በእኛ ላይ ገኖ መታየት በሌላ ጎኑ የእኛ መሞት ነው ።ኢየሱስ በእኛ ላይ መገለጥ የእኛ መሸፈን ነው ።

@ownkin
@cgfsd
Audio
ታላቁ ሊቀካህናት ኢየሱስ !!!

እንዲህ ያለ ሊቀካህናት ተገብቶናል ። ከወርቅ ይቅል አብዝት የነጠረ ወድ የሆነ ሊቀካህናት ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ ።


በፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለመኖር የግድ ኢየሱስን ማየት አስፈላጊ ነው ምክኒያቱም የእግዚአብሔር ፈቃድ በሙላት የኖረው ኢየሱስ ብቻ ነው ።

(ኢየሱስን በማየት በእግዚአብሔር ፈቃድ መመላለስ)

@cgfsd
@ownkin
እነሆ የተሰቀለው ክርስቶስ! እነሆ ለሁሉ በመስቀል የተገለጠው እግዚአብሔር !! 'እነሆ ሰውየው!' [ዮሐ.19፥ 6]

እግዚአብሔር ለማዳን የተገለጠበትን መንገድ ማጤን ግድ ይለናል ይላል ማርቲን ሉተር ። የቅዱሳት መጻሕፍትን ታሪክ ፍሰት ማመሳከሪያ በማድረግ እግዚአብሔር በዚህ ዓለም ለማዳን [ሰውን ከጠፋበት መንገድ ለመመለስና ለመታረቅ] ሲገለጥ ልክና ወሰን የለሽ ክብሩን በማሳየት አይደለም፤ ይልቅኑ በተቃራኒው ነበር ይለናል።

ሐዋርያቱም በአደባባይ የሰበኩት 'ንጉሡንና ወሰን የለሽ ክብር የተጎናጸፈውን' አይደለም። የተሰቀለውን እንጂ። አዚማሞቹንም የገላቲያ ማሕበራት 'ክርስቶስ በክብሩ በፊታችሁ ተስሎ አልነበረም ወይ?' አልተባሉም። 'እንደ ተሰቀለ' ተባሉ እንጂ። የተሰቀለውን ማሳየት ይቻላል፤ በመስቀል የደከመውን መስበክ የቤተክርስቲያን ኃላፊነት ነው። ዓለም ሞኝነት ያለችውን የማዳንና የመታደግ መንገድ ቤተክርስቲያን ጥበቤ ነው ትላለች። በክብር #እስኪገለጥ ሞቱን ትመሰክራለች።

'እነሆ ንጉሥሽ' የተባለውን ካላየን ሲሉ 'ከምድር ከፍ ከፍ ስል ሁሉን ወደኔ እስባለሁ' ብሎ ነበር ክርስቶስ። እነሆ መስቀሉ ለሁሉ የሚታይበት መንገዱ ነበረና።

ነገር ግን ባለጠጎችና 'ጸጋ ሞል' ነን የሚሉቱ መስቀል ጠል ናቸው። መስቀል ጠሎች ደግሞ 'እነሆ አምላካችን' ቢሉም የሚያሳዩት ወርቃቸውንና ብራቸውን ነው። ይዋሻሉ፤ ዋሾ ናቸው። መስቀል የተሰወረባት ማሕበር 'እነሆኝ' ብትል ታዳጊውንና በመስቀል የሞተውን አዳኝ አታሳይም፤ ሌላ ክርስቶስን ካልሆነ በስተቀር።

ማኀበራትም ሁለት ናቸው:- አንደኛይቱ በዚህ ዓለም የቆሰለውን አዳኝ ሳያፍሩ- የሚመሰክሩና ፈለጉን የሚከተሉ ያሉባት ናት። ኹለተኛይቱ ግን እንደ ዓለም ሁሉ በመስቀል ሞቱ የሚያፍሩ ያሉባት ናት።

እና የ'እነኾኝ' ጥሪዎች 'እነኾኝ መስቀል' ካላሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ጥበብ ይሰውራሉ። አጀንዳቸውም ሌላ ነው። ይኸው ነው።

#የተሰቀለው_ክርስቶሰ #የእግዚብሔር_ክርስቶስ #እግዚአብሔር_የሾመው_ንጉሥ


tegegn mulugeta

@ownkin
@cgfsd
በቃ መድህናችን እንዲህ ነው በመስቀል ላይ የተንጠለጠለ !!ተልዕኮው አድህኖት የነበረ በሰው ልብ፣ ያልታሰበው ግን በምክረ መለኮት የተበጀውን ታላቅ የሆነ የመስቀል ስራ ፈፀሞ በእጄ ያለን አዎ ጌታችን የተሰቀለው ነው በእርግጥም ነው ምንም የማናወላዳበት የማንዘነጋው የነፍስ ምስላችን ይሔው ነው ። እኛም መላልሰን ቤዛነቱን እንዘክራለን...ያ የተወጋው ጎኑ የተጠገንበትን፣ የፈሰሰው ደሙ የተሰማንበትን፣ በተቸነከረው እጁ ራሱ ቆርሶ ያጎረሰን ስጋ ሁሌ እንመለከታለን

መሲሁን ኢየሱስ እርሱ ዘወትር እንደተሰቀለ እንድናስብ መንፈስ ቅዱስ ይርዳን ።


@ownkin
@cgfsd
(ኢየሱስ ታዛዬ )


የጌታ ኢየሱስን ፍለጋ እንደመከተል ለልብ አንጀት የሚያደርስ ጥም ቆራጭ ህይወት ከወዴት ይገኛል ??
ኢየሱስ ምድር ላይ የረገጠ አንድ ተራ ሰው ብቻ አልነበረም መለኮትም እንጂ ። ምናልባት ባደገበት አውራጃ የማያውቁት ከማርያም ቤት የቀደመ በኩር ልጅ ብቻ አድርገው የሚመለከቱ አይጠፉም ሌሎችም ደግሞ በሙያው አናፂ የሆነ አንድ ወጣት የሚያደርጉት አይታጡም ።. አገልግሎቱን ሀ ብሎ ከዩሀንስ ጥምቀት በኋላ አስከትሎ ሲጀምር ነቢይ ፣መምህር ግፋ ቢል የአይሁድ የተበላሸ ፖለቲካ የሚያስተካክል መሲህ አድርገው ያስቡት ነበር ። እርሱ ግን ያነገበው ተልዕኮ ፣ የመጣበት መምጣት ፣ ራሱን ያስኬደበት ማስኬድ በእጅጉ አብዝቶ የብዙዎች ቀልብ ያሽፍታል ።

ኢየሱስ ታዛ ነው !!!! ታዛ መጠለያ ፣ መሸሸያ ፣መኖሪያ ፣ ማረፊያ የሚል ትርጓሜ አለው ። ጌታ ደቀመዛሙርቱን ወደራሱ ጠራቸው ይላል ቅዱስ ቃሉ ። በሌላ አነጋገር ኢየሱስ ወደ ማንነቱ ጠራቸው እንደማለት ነው ። ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን ሲጠራቸው እነሱን ለማኖር ወደሚሆን ቅንጡ ፣ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶች ፣ ቤተመንግስት ፣ ሰፋፋ ወዳለው ክፍሎች አይደለም ወደራሱ የጠራቸው ወደ እሱነቱ ወደ ክርስቶስነቱ ፣ ወደ አሳራፊቱ ነው የጠራቸው የሚያርፉት በኢየሱስ ላይ ነው ኑሮአቸው የተመሰረተው በእሱነቱ ላይ ነው ።

ደቀመዛሙርቱን ሲጠራቸው ሆድ ያዝ ያዝ የሚያረጉ አሉ የተባሉ ምግቦችን ሜኑ እያስነባባቸው አለነበረም ..ዲዘርት ፣አቢታይዘር ፣ስጋ ፣አትክልት እያማረጡ እንዲበሉት አልነበረም ።እሱ ግን የጠራቸው ወደ ማንነቱ ነበር የህይወት እንጀራ ወደ ሆነው ማንነቱ ቢበሉት ወደማያልቀው አንዴ አይደለም ዘላለም የሚያጠግብ ስጋው በመስቀል ላይ ቆርሶ ደሙን አፍስሶ እንኩ ብሉኝ ወዳለበት የህይወት ጥሪ የው የተጣራው ።

ደቀመዛሙርት ኢየሱስ ሲከተሉት በወቅቱ እስራኤል ላይ የፖለቲካ ስጋት ነበር ኑ ሲል ወታደር መድቦላቸው ከፖለቲካ ሊከላለከላቸው ከሞት ሊያስመልጣቸው ሳይሆን ራሱ ጠባቂ፣እረኛ ሊሆናቸው ህይወት፣ ትንሳኤ ሁኗቸው ሞት እንዲያሸንፉ ነበር ።

ታዛ ኢየሱስ ነው!!ማንነቱ መጠለያ !!በማንነቱ የተጠለልን ማንነቱ ጥላ የሆንነ ሰዎች ነን!!


ፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
(ለጌታ መቸኮል)


ችኩሉ ጴጥሮስ ......... ችኮላ መቸም ከሰው ልጅ አብራክ የተፈበረከ ባህሪ ነው ። የሰው ልጆች በሞላ የጋራ የሚያረገው ባህሪ ችኮላ አንዱ ነው ፤ ምን ለማለት ነው ጴጥሮስ ብቻ ችኩል ያደረገው ማን ነው ?? በእርግጥ ጴጥሮስ ችኩል ለመሆኑ መፀሀፍ ቅዱሳችን ገልጦ ያሳየን ሀቅ ነው ። አንዳንዴ የጴጥሮስ ችኮላ ሲያጠፋ ቢስተዋልም ግን መቸኮሉ ለጌታ ነው ። ለጌታ ነው የቸኮለው የሚያሰኙን አንድ ሁለት ብለን የምንጠቅሳቸው ስራዎቹ እናያለን ።
ምናልባትም ጌታን ከተከተሉት አስራ ሁለቱ ሐዋሪያት በእድሜ ገፋ ያለው እሱ ሳይሆን አይቀርም ቢሆንም ግን ያለው ትኩስነት ልጅ ነው እንዴ ያስብላል ።
ኢየሱስ ጴጥሮስ በተደጋጋሚ ገስጿታል በተደጋጋሚም ደግሞ በተቀራኒው ምላሽ ሰጥቶታል ግን አንድ ነገር ጴጥሮስ ላይ ይስተዋላል መቸኮል አዎ ግንም ደግሞ ለጌታ መቸኮል ።

የመፀሀፍ ቅዱስ አስተማሪዎች በጴጥሮስ ታሪክ ዙሪያ የተሰራውን አፈ ታሪካ እንዲህ ይናገራሉ " ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን ድንጋይ ይዛችሁ ተከተሉኝ ይላል ሁሉም ትላልቅ ድንጋይ ይዛሉ ጴጥሮስ በተራው ጠጠር ይይዛል ረጅም ከተጓዙ በኋላ ትንሽ እንዲያርፉ ያረግ እና የያዙትን ድንጋይ ወደ ዳቦ ይይረዋል የሁሉም በያዙት ድንጋይ ልክ ትልልቅ ዳቦ(ድፎ ዳቦ) ሲሆን የጴጥሮስ ጠጠር ስለነበረች ዳቦ ቆሎ ትሆናለች ። ሁሉም ይበሉና ይጠግባሉ ጴጥሮስ ግን ያዝናል ከእንደገና ጌታ ድንጋይ ይዛችሁ ተከተሉ ይላል ሁሉም ስለጠገቡ በተራቸው አነስተኛ ጠጠር ይይዛሉ ጴጥሮስ ግን ትልቅ ይይዛል በኋላ ከተቀየረ ካሳ እንዲሆነው ከብዙ ጉዞ በኋላ ጌታ በሉ የያዛችሁት ድንጋይ ወርውሩ ይላቸዋል ይወረውራሉ ጴጥሮስ እንደተጨበቀው ሳይሆንለት ይቀራል ያዝናል ። "
(ልብ በሉ ይሔ ታሪክ ለማስተማር ብቻ የሰራ ነው )

ከዚህ አፈ ታሪክ ጠቅሰው ጴጥሮስ ችኩል ነው ይተላለፋል በርካቶች ይላሉ ጌታ ግን እንደዚህ የሚለው ይመስለኛል ጴጥሮስ ለኔ ነው የቸኮለው ።

3 ጊዜ የካደው ክህደት ካሃዲነቱ ትዝ ይለናል ጌታ ደግሞ ለመመለስ አብዝቶ ያነባውን እንባ ያስታውሳል ። የማልኮስ ጆሮ እንደቆረጠ እናስታውሳለን ጌታ ግን ለቤተክርስቲያን መሪነት ያየዋል ።

አጎል መቸኮል ሳይሆን ለጌታ መቸኮል ግን እንዴት ያስደስታል ስለ ጌታ ተልዕኮ ፣ ስለ ጌታ የልብ ሃሳብ መቸኮል ግን እንደምን ያረካል !!
እንደዚህ አይነት ችኮለ ይብዛልን ጌታን ከመውደድ፣ ለአካሉ ለቤተክርስቲያን ከማሰብ ፣ወንጌል ከማድረስ፣ ክርስቶስ እንደተቆረሰ እንደ እሱ ለሌሎች ለመቆረስ ይብዛልን።

ለጌታ መቸኮል


ፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
መስቀሌ በገዘፈብኝ ጊዜ ሁሉ መስቀልህን አሳየኝ ጌታዬ

jonny afework

@ownkin
@cgfsd
#ሩጫ ሲበዛ ባክኜ እንዳልቀር #በማርታ ዘመን ላይ እንደ ማርያም ልኖር #ኢየሱስ አንተ ላይ እደላደላለሁ #መድኔ አንተ ጋር አብዝቼ ቆያለሁ

@ownkin
@cgfsd
የወደድኩት ምስክርነት



"እሰከ ዛሬ ኢየሱስ ኢየሱስ ሲሉ ጥያቄ ይሆንብኝ ነበር ። በጌታ ነኝ ግን አብዛኛው እንደ ታሪክ ነበር የምመለከተው ። ነገር ግን ክርስቶስ የሆነው መሆን የከፈለው ዋጋ በክርስቶስ ያገኘሁትን ማንነነት ሲገባኝ  መፀሀፍ ቅዱስ በናፍቆት ማንበብ ጀመርኩ በጉጉት መፀለይ ቀጠልኩ ..መኖር መኖር ጓጓሁ ፍቅሩ ጨመረብኝ  ። "


   @ownkin
  @cgfsd
ክርስቶስ አልዓዛርን በታላቅ ድምጽ ጮኾ "ወደ ውጭ ና!" ብሎ ከጥልቅ እንቅልፉ እንደቀሰቀሰው ጳውሎስም በመልዕክቱ "አንተ የምትተኛ ንቃ!" በማለት ሰውን ከጥልቅ እንቅልፉ ይቀሰቅሳል።

ሰው የሚነቃው በዝግመተ-ለውጥ ሳይሆን በክርስቶስ ነው፡ ክርስቶስ የሰውን ዘር የማንቂያ ደውል ነው፡ ሰው ከጨለማ ከጥልቁ የሚወጣው በክርስቶስ ብቻ ነው፣ ምክንያቱም አንተ የምትተኛ ንቃ ካለ በኃላ ክርስቶስም #ያበራልሃል ነው የሚለው።

ዮሃንስም በወንጌሉ በአልዓዛር አስታኮ የሰው ዘር ሁሉ እንዳንቀላፋ እየነገረን ነው፡ ለዚህም ነው ጌታችን፦

"ወዳጃችን አልዓዛር ተኝቶአል፣ ነገር ግን ከእንቅልፉ ላስነሣው እሄዳለሁ" ያለው።

ሰው ሁሉ ተኝቶአል ነገር ግን ክርስቶስ የማስነሳት አቅም አለው።

ጳውሎስም ምንም እንኳን ለኤፌሶን አማኞች ቢጽፈውም መልዕክቱ ግን ለሰው ሁሉ ነው፡ ምክንያቱም ሰው ያለ ክርስቶስ "እንቅልፋም" ነው፡ ስለዚህም ንቃ! ይላል ጳውሎስ።

ሰውን ዝግመተ-ለውጥ ወይም ቴክኖሎጂና ሳይንስ አያነቃውም ክርስቶስ እንጂ፡ እርሱ ወደ ዓለም የመጣው ብርሃን ነው ምንም እንኳን ሰው ስራው ክፉ መሆኑን አውቆ ቢደበቅም፤ ልክ አዳም በዛፍ እንደተደበቀው።

ክርስቶስ የሰውን ሁሉ ጨለማ ያበራል!!!

Yilu danu

@ownkin.
@cgfsd
እንደራሱ ቁስል ህመሜ የሚያመው
የኔ ሊቀ ካህን ኢየሱስ ብቻ ነው

Kaleab Tsegaye 🙏

@ownkin
@cgfsd
( ጌታዬ ኢየሱስ)


*የማደምቀው ጌታ የለኝም በሞቱ ያደመቀኝ እንጂ
* የምኩለው አዳኝ የለኝም በደሙ የኳለኝ እንጂ
* የማካፍለው አምላክ የለኝም በትንሳኤው ያካፈለኝ እንጂ
* ወድጄ የፈለገኩት መሲህ የለኝም የወደደኝ እንጂ

@ownkin
@cgfsd
በኢየሱስ በማመናችን ምክንያት እግዚአብሔር በእኛ፣ እኛ ደግሞ በእግዚአብሔር መኖር ጀመርን።መለኮት በእኛ ውስጥ ኖረ።እኛ ደግሞ በመለኮት ህልውና ውስጥ ኖርን።
ዋው ይሄ በእውነት ድንቅ ነገር ነው።😍😍🙏🙏🙏

ከገፅ የተወሰደ

@ownkin
@cgfsd
ኢየሱስን ለመናፈቅ ከህልውናው የተሻለ አንድም ነገር የለም ። በህልውናው ውስጥ የክርስቶስን ፍቅር ያንሰፈስፈናል .. በህልውናው ውስጥ ጎልጎታ የትናንት ያክል ቅርብ ያረገዋል ..ቀራኒዮን የዛሬን ያክል ያሳያል ..በህልውናው ውስጥ ኢየሱስ የሚለው ስም ተጠርቶ አይጠገብም ..በህልውናው ውስጥ እኔነት ፀጥ ይላል .. በህልውናው ውስጥ የኢየሱስ መምጣት በጉጉት ያስናፍቃል ያስጠብቃል ..በህልውናው ውስጥ የክርስቶስ ሞት እና ትንሳኤ ተነስቶ አይጨረስም ..በህልውናው ውስጥ የክርስቶስ ደም ትርጉም ይሰጣል..በህልውናው ውስጥ የኢየሱስ ልብ ጮኽ ብሎ ይሰማል ..በህልውናው ውስጥ ኢየሱስ ያረካል..በህልውናው ውስጥ ኢየሱስ ብቻ ..በህልውናው ውስጥ የሞተልን፣የተሰቀለልን፣ የተሰቃየልን እርሱ ብቻ ይደምቃል ..


@ownkin
@cgfsd
ዉዴ ለእኔ ያለዉን የፍቅር መግለጫ የጻፈው በስጋና በደሙ ቀራኒዮ ነበር ፍቅሩ ደግሞ ከመቃብር በላይ ነው።

#ኢየሱስ

sharona

@ownkin
@cgfsd
የመስቀሉ ፍቅር ለየት ያረገው ዘላለማዊ መሆኑ ነው ።ዘላለማዊ መሆኑ ደግሞ እያደር የማይቀዘቅዝ፣የማይበርድ ፣የማይሰበር የወደዳቸውን እስከ መጨረሻው የሚያስወድድ ፍቅር ነው ። ለተካፈለው ደግሞ በዘላለለም ውስጥ ሁልጊዜ ዘላለማዊን ፍቅር እያወቁ የሚያስኖር ነው ። የመስቀሉ ፍቅር የአንድ ጊዜ ክስተት አይደለም ዘላለማዊ እንጂ ። ይሔ ዘላለማዊ ፍቅር በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት በደሙ ተፃፈ ፣ በደሙ ተበሰረ ፣ በደሙ ተተረከ፣ በደሙ ታየ ... በደሙ የፍቅሩን ጥንካሬ ፣ብርታት ፣ውበት ፣መልክ ፣ልክ አሳየን ... ለዚህ ነው ደሙ ፍቅሩ ላይ እርግጠኛ ያረገን .. የእኛ ጌታ ውዳችን ኢየሱስ በአንደበቱ ሳይሆን በደሙ የነገረን ፍቅር ሰምተናል ..በእርግጥም ይወደናል ።
(ጠበቃ አለን!!!)

ጠበቃ ብሎ በግሪከኛው ጵራቅሊጦስ ይለዋል ። ጵራቅሊጦስ  ለመንፈስ ቅዱስ የተሰጠ ስም ነበር አፅናናኝ ማለት ነው ።ሌላኛው ትርጉሙ እዚህ ጋር የተጠቀሰው ጵራቅሊጦስ በጥብቅናው  የሚታይ ፣ክስ የሚያስወግድ ጠበቃ  ነው  ። የድሮ የመፀሀፍ ቅዱስ ቅጅ ጠበቃ የሚለውን የሚከራከርልን ይላል ምናልባት እኛን የወከለ ብቁ የሆነ ተከላካይ ነው ።ማስተዋል ያለብን ኢየሱስ ጵራቅሊጦስ ተብሎ የተጠራበትን እውነት እና ምክኒያት ይሆናል።(1ዩሀ2:2-3)

ኢየሱስ ብቸኛ  የማይከራከር ጠበቃ ነው ምክኒያቱም ደግሞ ደሙ የታመነ ምስክር ነው። ደሙ ራሱ ይመሰክራል የታመነ ምስክር በንፁሁ ደም በኩል አቅርቧል  ። የእኛ ጠበቃ አያሳፍርም የታመነ ደም አለው እርሱን ደሙን ጥብቅና ስለቆመላቸው  አሳይቷል ። ጠበቃ የሚያቀርበው አንዳች ማስረጃ የተከሰሰውን አካል ነፃ የሚያወጣ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርበታል የእኛ ጠበቃ ጌታችን ኢየሱስ ያቀረበው ማስረጃ ደሙን ነው ይሔው እኔ ሙቻለሁ ስለ እርሱ በደል ተሰውቻለው ሞታቸውን በሞቴ ወስጃለሁ በቀራኒዮ ላይ አልፊያለሁ እኔ እንደዚህ የሆንኩት የእነርሱን እዳ ለመክፈል ነው እና ይሔው ንፁህ ደሜ እነርሱ ከእኔ እንከን አልባ ንፁህ ደም የተነሳ ንፁህ ናቸው የሚል ማስረጃ አቅርቧል ።

ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን ሲባል የብሉይን ስርአት ማስታወስ አለብን .. ምሳሌ በመፀሀፍ ቅዱስ ውስጥ ሰዎች ሀጢያት ሲያደርጉ ወይም ባያደርጉ የሚከሳቸው ከሳሽ ነበር ። ኢዮብ 1... ኢዩብን ለመጣል በእግዚአብሔር ፊት ሰይጣን ከሳሽ ሆኖ ቀርቧል እዬብን በማጣጣል በእግዚአብሔር ፊት እደ ከሳሽ ቁሟል ።
ሌላው ታላቁ ካህን ኢያሱ (ዘካ3&4) ካህኑ ኢያሱ የለበሰው ልብስ ቆሽሾ ነቀፋ ተገኝቶበት በእግዚአብሔር ፊት ከሳሽ ሁኖ ሰይጣን ቆመ ። አሁን ግን ክሱ ስለተዘጋ ከሳሽ ሁኖ አይቆም ለምን ሲባል አሁን ጠበቃው ነው የቆመው ለከሽ መዝገቡ ተዘግቷል አበቃ ካላስ ጠበቃ አለን ።የወንድሞች ከሳሽ ተጥሏል("ራዕ 11) አሁን ከሳሼን ሳይሆን ጠበቃዬን ነው ማስበው ..እዚህ ጋር ማስተዋል ያለብን ዋና ነገር ጠበቃ አለን በማለት በሀጢያት መመላለስን ሳይሆን ጠበቃ አለን ብለን ጠበቃችን ዋጋ ለከፈለበት ክቡር እና ቅዱስ ደም በፅድቅ መኖር ነው ።

ይሔ ጠበቃ ፃዲቅ ነው ። ስራው ትክክል ነው ጠበቃው ፃዲቅ ነው። 


ፊሊሞን ነጋ
@ownkin
@cgfsd
ሁልጊዜ የማስተውለው አንድ ባለ ጋሪ  ነበር ። የፈረሱን አይኖች አራት በአራት በተከረከመ የጄሪካን ቁራጭ   ወደ ጎን እንዳይመለከት አይኖቹን ይሸፍነዋል ። በመሆኑም ፈረሱ ወደ ግራም ሆነ ወደ ቀኝ አያማትርም የፊት ለፊቱን ብቻ እየተመለከ ይጓዛል ።

  ይሔ እውነት በተለይም ክርስቶስ ኢየሱስን አምኖ ዳግም ለተወለደ ክርስቲያን የግድ ግድ አስፈላጊ ነው  ። ወደ ግራም ወደ ቀኝም በሄድንበት በሙሉ አይናችን እንዳንኳትን ፣ ያየነው ሁሉ እንዳያምረን ፣ በመንገድ ሁሉ እየተደነቅን ፣  እየተገረምን እንዳንቆም በአይኖቻችን ዙሪያ የሚከል አንድ ወሳኝ ጉዳይ ያስፈልጋል ፤ እሱም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ነው ። የክርስቶስ መስቀል ወደ ሌላ ቦታ እንዳንመለከት ይከልለናል ፣ ሁሉን ጉዳይ ያቀልብናል ፣ የክርስቶስ ፍቅር ፣ ይቅርታ ፣ ምህረት ፣ መወደድ ፣ ፅድቅ ፣ ቅድስና ሁሉ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል ..ያኔ ሁሉ በአይናችን ፊት ይቀላል ፣ እንደምናምንቴ እንድናይ ያረጋል ። የክርስቶስ መስቀል አለምን ፣ ሰይጣን ፣ ሀጢያት ፣ ሞት እንዳናይ የተለያየንበት የእግዚአብሔር የመንግስት ሚስጥር ፣ ፈቃድ ፣ ዕቅድ ፣ ህብረትን እንድንረዳ እና እንድንመለከት ያግዛል ።




@ownkin
@cgfsd
ፀጋ በህይወታችን ፀጋነቱ የሚታወቀው በእኛ በኩል ያለው ድካም በክርስቶስ ስራ በመሸፈኑ ነው ።
          (የዱባ ጥጋብ)


@ownkin
@cgfsd