በክርስቶስ ( in christ)
694 subscribers
98 photos
34 videos
41 files
37 links
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Download Telegram
ክርስቶስ አልዓዛርን በታላቅ ድምጽ ጮኾ "ወደ ውጭ ና!" ብሎ ከጥልቅ እንቅልፉ እንደቀሰቀሰው ጳውሎስም በመልዕክቱ "አንተ የምትተኛ ንቃ!" በማለት ሰውን ከጥልቅ እንቅልፉ ይቀሰቅሳል።

ሰው የሚነቃው በዝግመተ-ለውጥ ሳይሆን በክርስቶስ ነው፡ ክርስቶስ የሰውን ዘር የማንቂያ ደውል ነው፡ ሰው ከጨለማ ከጥልቁ የሚወጣው በክርስቶስ ብቻ ነው፣ ምክንያቱም አንተ የምትተኛ ንቃ ካለ በኃላ ክርስቶስም #ያበራልሃል ነው የሚለው።

ዮሃንስም በወንጌሉ በአልዓዛር አስታኮ የሰው ዘር ሁሉ እንዳንቀላፋ እየነገረን ነው፡ ለዚህም ነው ጌታችን፦

"ወዳጃችን አልዓዛር ተኝቶአል፣ ነገር ግን ከእንቅልፉ ላስነሣው እሄዳለሁ" ያለው።

ሰው ሁሉ ተኝቶአል ነገር ግን ክርስቶስ የማስነሳት አቅም አለው።

ጳውሎስም ምንም እንኳን ለኤፌሶን አማኞች ቢጽፈውም መልዕክቱ ግን ለሰው ሁሉ ነው፡ ምክንያቱም ሰው ያለ ክርስቶስ "እንቅልፋም" ነው፡ ስለዚህም ንቃ! ይላል ጳውሎስ።

ሰውን ዝግመተ-ለውጥ ወይም ቴክኖሎጂና ሳይንስ አያነቃውም ክርስቶስ እንጂ፡ እርሱ ወደ ዓለም የመጣው ብርሃን ነው ምንም እንኳን ሰው ስራው ክፉ መሆኑን አውቆ ቢደበቅም፤ ልክ አዳም በዛፍ እንደተደበቀው።

ክርስቶስ የሰውን ሁሉ ጨለማ ያበራል!!!

Yilu danu

@ownkin.
@cgfsd