ፀጋ በክርስቶስ ቤዛነት ስራ እንድንመካ 💪 ያደርጋል !! በእርግጥ ፀጋ እንዲሁ በነፃ ይሰጥ እንጂ "እንዲሁ" እንዲሰጥ ትልቁ ዋጋ ከፍሎ ሂሳባች ያወራረደው ክርስቶስ ነው በቤዛነቱ አማካኝነት ፤ ለእኛ እንዲሁ በነፃ ነው ለክርስቶስ ግን የሞት ዋጋ ፣ ቤዛነት አለበት ። ስለዚህ በክርስቶስ ቤዛነት ዋጋ መክፍል ፀጋው እንዲሁ ስለተሰጠ ! ፀጋው የክርስቶስን የቤዛነት ስራ ያጎላል ፣ ጮክ ብሎ ይናገራል 🗣 ፀጋ ሲነሳ የክርስቶስን ያ ድንቅ የመስቀል ስራ ሁልጊዜ ይነሳል ።
@cgfsd
@ownkin
@cgfsd
@ownkin
የኢየሱስ የማንነቱ ማረጋገጫ ራሱ ነው ። እርሱ መፅሀፍ አልፃፈም ፣ የሚመራው የጦር ሀይል አልነበረውም ፣ የፖለቲካ ስልጣን አልጨበጠም ፣ ወይም የሀብት ማማን አልተቆናጠጠም ። በምድር ላይ አገልግሎቱ፥ ከኖረበት መንደር በአንድ መቶ ኪሎ ሜትር የርቀት ወሰን ውስጥ ነበር የተመላለሰው ። ነገር ግን ፥ አቻ ያልነበረው ሕይወቱ ፥ልብ ሰርስሮ የሚገባው ትምህርቱና እጅ በአፍ የሚያስጭኑት ስራዎች የሰዎችን ትኩረት ስበው አምነውበት እንዲከተሉት ወይም እንዲቃወሙት ያስገድዱ ነበር ።
የተቆረሱ ነፍሶች
@cgsfd
የተቆረሱ ነፍሶች
@cgsfd
እግዚአብሔርን የምናውቀው በተገለጠልን ልክ ነው የእግዚአብሔር የመገለጥ ልክ ደግሞ ኢየሱስ ። የብሉይ ኪዳን አባቶች ሳይቀሩ እግዚአብሔር ይረዱት የነበረው በተገለጠላቸው መጠን ነበር ። ለአብርሃም አልሻዳይ፣ ለሙሴ ያህዌ ብሎ በነገራቸው መሰረት ተረዱት ። ነገር ግን ይሔን እግዚአብሔር በትክክል ለመግለጥ ኢየሱስ መገለጡ አስፈላጊ ነው ። ኢየሱስ የመገለጥ ወኪል ነው እግዚአብሔርን የተረዳትበት የመጨረሻ መንገድ እሱ ብቻ ነው ። ኢየሱስ የመጨረሻው የእግዚአብሔር ግልጠት ነው ። እግዚአብሔር ብቻ ሳይሆን ራሳችንም የምናውቀው በኢየሱስ በኩል በክርስቶስ ኢየሱስ ባገኘነው ማንነት ማንነታችን በኢየሱስ በኩል እናውቃለን ።
@cgfsd
@ownkin
@cgfsd
@ownkin
#የክርስቶስ_ግርፋት
#በምሁሩ_ዕይታ
#ክፍል_1
የወዙ እንደ ደም ነጠብጣብ መሆን፥ ይሄ ሁኔታ በህክምናው ዓለም ሄማትድራሲስ በመባል ይታወቃል። ብዙም የተለመደ አይደለም፤ ነገር ግን ከፍተኛ ከሆነ ሥነልቦናዊ ጫና ጋር የሚያያዝ ሁኔታ ነው።
ከባድ ወይም ከመጠን ያለፈ ጭንቀት ላብ እንዲመነጭ በሚያደርጉ እጢዎች ውስጥ የሚገኙትን ደም ስሮች የሚጎዱ ኬሚካሎች እንዲረጩ ያደርጋል። በዚህም በእነዚህ እጢዎች ውስጥ ጥቂት የደም መፍሰስ ይፈጠራል። ስለዚህ ከሰውነት የሚወጣው ላብ ከደም ጋር የተዋሃደ ይሆናል። ይህም ሲሆን ብዙ የደም መፍሰስ ይኖራል ማለት አይደለም፤ ነገር ግን ጥቂት ደም ከላብ ተቀላቅሎ ይገኛል።
ይህ ክስተት የሰውነት ቆዳን ስስና ደካማ ያደርገዋል፤ ኢየሱስም በቀጣዩ ቀን በሮማውያን ሲገረፍ የሰውነቱ ቆዳ እጅግ ደካማ ሆኖ ነበር። የሮማውያን ግርፊያ እጅግ ጭካኔ የተሞላበት እንደሆነ ይታወቃል። ተለምዷዊው ግርፋት 39 ግርፋት ያህል ነው። ብዙውን ጊዜ ግን ከዚህም ሊበልጥ ይችላል፤ በተለይም ደግሞ ገራፊው ወታደር እንዳለበት ሙድ ወይም ስሜት ሊለዋወጥ ይችላል።
አንድ የሮማ ወታደር ለግርፊያ የሚጠቀመው ጅራፍ ከቆዳ የተሰፋ እና ትንንሽ የማይባሉ የብረት ኳሶች የታሰረበት ጅራፍ ነው። አንዱ ግርፋት ሰውነት ላይ ሲያርፍ እነዚህ የብረት ኳሶች ጥልቅ ቁስል እና ጉዳት ያመጣሉ፤ በኋላም ግርፋቱ ሲደጋገም ከቁስለት ያልፍና የሰውነት ቆዳ እየተከፈ ይሄዳል። ጅራፉ የአጥንት ስብርባሪዎች ጭምር አብሮ የተሰፋበት ሲሆን፥ በሚዘገንን ሁኔታ የሰውነትን ቆዳ ይጎዳሉ።
ይህ ግርፋት የሚደርስበት ሰው ጀርባ፥ ግርፋቱን ተከትሎ ከሚፈጠሩት ትልልቅ ክፍተቶች የተነሳ ሊቦጫጨቅ የሚችል በመሆኑ የጀርባ አጥንት የተወሰነው ክፍል ሳይቀር ሊታይ የሚችልበት አጋጣሚ ይፈጠራል። ግርፋቱ ከትከሻ አንስቶ እስከ ታችኛው ጀርባ፥ አልፎም መቀመጫን እና የእግር ታፋ ጀርባን ሳያስቀር ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል። እጅግ አሰቃቂ ነው።
የሮማውያንንን ግርፍያ ያጠና አንድ ፊሲሺያን "ግርፋቱ እየቀጠለ ሲሄድ፥የቁስሎቹ መቀደድ ወደታችኛው የአጥንት ጡንቻ ድረስ በመዝለቅ እንደደም የሚፈስ የተቦጫጨቀ ሥጋን ይፈጥራል።
ዩሴቢየስ የተባለ በሶስተኛው ክፍለዘመን የነበረ አንድ የታሪክ ምሁር የግርፋቱን ሁኔታ ሲያስረዳ "ይህ መከራ የሚደርስበት ሰው ደም ሥሮቹ፥ ጡንቻዎቹ፥ ጅማቶቹ እና አንጀቱ ሳይቀር ከግርፋቱ የተነሳ ለዕይታ ተጋላጭ ይሆናሉ።
ተገርፈው እንዲሰቀሉ ታልፈው የሚሰጡ ብዙዎቹ ፍርደኞች መስቀሉ ጋር ሳይደርሱ ከግርፋቱ የተነሳ ብቻ ሟቾች ናቸው። በመጨረሻም የሚገረፈው ሰው በቃላት ሊገለፅ ከሚችለው በላይ የሆነ ሕመምን በማስተናገድ ወደ ሃይፖቮለሚክ ሁኔታ ይገባል።
ሃይፖ ማለት "ትንሽ" ሲሆን ቮል (ቮልዩም) ማለት "መጠን" ወይም "ይዞታ" ማለት ነው፤ ኢሚክ ማለትም "ደም" ማለት ነው። ስለዚህ የሃይፖቮለሚክ ሁኔታ ብዙ የደም መፍሰስ የገጠመውን ሰው የሚያመላክት ሁኔታ ነው።
ይሄም ሁኔታ አራት ነገሮችን ይፈጥራል።
አንደኛ፦ ብዙ ደም ቢፈስም የደም ዝውውሩን ለማስቀጠል የልብ ምት በፍጥነት እየጨመረ ይሄዳል።
ሁለተኛ፦ የደም ግፊት ይወርዳል። ይህን ተከትሎ ራስን ስቶ መውደቅ ይፈጠራል።
ሶስተኛ፦ ኩላሊቶች የፈሳሽ ማጣራት ስራን መስራት ያቆማሉ። ይህም በብዙ ደም መፍሰስ ምክንያት ብዙ ፈሳሽ ከሰውነት ስለወጣ ተጨማሪ ፈሳሽ እንዳይወጣ ለማድረግ ነው።
አራተኛ፦ ሰውነት በደም መፍሰስ ምክንያት ያጣውን ፈሳሽ ለመተካት ከፍተኛ የሆነ የውሃ ጥማት ይፈጠራል።
ኢየሱስም አንደኛውን የመስቀሉን ክፍል ተሸክሞ ወደ ቀራንዮ በሚወጣበት ጊዜ በሃይፖቮለሚክ ሁኔታ ውስጥ ገብቶ ነበር። በመጨረሻም ኢየሱስ ራሱን ስቶ በመውደቁ የሮማው ወታደር ስምኦንን መስቀሉን እንዲሸከምለት አዘዘው። በኋላ ላይም ኢየሱስ "ተጠማው" ሲል እና ወይን ሲሰጠው እናነባለን።
ግርፋቱ ካደረሰበት ከባድ ጉዳት የተነሳም ኢየሱስ ገና የሚሰቀልባቸው ሚስማሮች በእጆቹ እና በእግሮቹ ከመቸንከራቸው አስቀድሞ እጅግ አሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ ሊሆን እንደሚችል ምንም ጥያቄ የለውም።
ዘ ኬዝ ፎር ክራይስት (The Case for Christ)፥ 1998 እ.አ.አ
ሊ ስትሮቤል ከ ዶ/ር አሌክሳንደር ሜዜሬል ጋር ካደረገው ቃለምልልስ የተወሰደ
ለዚህ ልጥፍ እንዲመች ተደርጎ የተዘጋጀ
ከገፅ 194-196
በጌታ በኢየሱስ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው!!!
✍Kdus zewdu
@cgfsd
#በምሁሩ_ዕይታ
#ክፍል_1
የወዙ እንደ ደም ነጠብጣብ መሆን፥ ይሄ ሁኔታ በህክምናው ዓለም ሄማትድራሲስ በመባል ይታወቃል። ብዙም የተለመደ አይደለም፤ ነገር ግን ከፍተኛ ከሆነ ሥነልቦናዊ ጫና ጋር የሚያያዝ ሁኔታ ነው።
ከባድ ወይም ከመጠን ያለፈ ጭንቀት ላብ እንዲመነጭ በሚያደርጉ እጢዎች ውስጥ የሚገኙትን ደም ስሮች የሚጎዱ ኬሚካሎች እንዲረጩ ያደርጋል። በዚህም በእነዚህ እጢዎች ውስጥ ጥቂት የደም መፍሰስ ይፈጠራል። ስለዚህ ከሰውነት የሚወጣው ላብ ከደም ጋር የተዋሃደ ይሆናል። ይህም ሲሆን ብዙ የደም መፍሰስ ይኖራል ማለት አይደለም፤ ነገር ግን ጥቂት ደም ከላብ ተቀላቅሎ ይገኛል።
ይህ ክስተት የሰውነት ቆዳን ስስና ደካማ ያደርገዋል፤ ኢየሱስም በቀጣዩ ቀን በሮማውያን ሲገረፍ የሰውነቱ ቆዳ እጅግ ደካማ ሆኖ ነበር። የሮማውያን ግርፊያ እጅግ ጭካኔ የተሞላበት እንደሆነ ይታወቃል። ተለምዷዊው ግርፋት 39 ግርፋት ያህል ነው። ብዙውን ጊዜ ግን ከዚህም ሊበልጥ ይችላል፤ በተለይም ደግሞ ገራፊው ወታደር እንዳለበት ሙድ ወይም ስሜት ሊለዋወጥ ይችላል።
አንድ የሮማ ወታደር ለግርፊያ የሚጠቀመው ጅራፍ ከቆዳ የተሰፋ እና ትንንሽ የማይባሉ የብረት ኳሶች የታሰረበት ጅራፍ ነው። አንዱ ግርፋት ሰውነት ላይ ሲያርፍ እነዚህ የብረት ኳሶች ጥልቅ ቁስል እና ጉዳት ያመጣሉ፤ በኋላም ግርፋቱ ሲደጋገም ከቁስለት ያልፍና የሰውነት ቆዳ እየተከፈ ይሄዳል። ጅራፉ የአጥንት ስብርባሪዎች ጭምር አብሮ የተሰፋበት ሲሆን፥ በሚዘገንን ሁኔታ የሰውነትን ቆዳ ይጎዳሉ።
ይህ ግርፋት የሚደርስበት ሰው ጀርባ፥ ግርፋቱን ተከትሎ ከሚፈጠሩት ትልልቅ ክፍተቶች የተነሳ ሊቦጫጨቅ የሚችል በመሆኑ የጀርባ አጥንት የተወሰነው ክፍል ሳይቀር ሊታይ የሚችልበት አጋጣሚ ይፈጠራል። ግርፋቱ ከትከሻ አንስቶ እስከ ታችኛው ጀርባ፥ አልፎም መቀመጫን እና የእግር ታፋ ጀርባን ሳያስቀር ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል። እጅግ አሰቃቂ ነው።
የሮማውያንንን ግርፍያ ያጠና አንድ ፊሲሺያን "ግርፋቱ እየቀጠለ ሲሄድ፥የቁስሎቹ መቀደድ ወደታችኛው የአጥንት ጡንቻ ድረስ በመዝለቅ እንደደም የሚፈስ የተቦጫጨቀ ሥጋን ይፈጥራል።
ዩሴቢየስ የተባለ በሶስተኛው ክፍለዘመን የነበረ አንድ የታሪክ ምሁር የግርፋቱን ሁኔታ ሲያስረዳ "ይህ መከራ የሚደርስበት ሰው ደም ሥሮቹ፥ ጡንቻዎቹ፥ ጅማቶቹ እና አንጀቱ ሳይቀር ከግርፋቱ የተነሳ ለዕይታ ተጋላጭ ይሆናሉ።
ተገርፈው እንዲሰቀሉ ታልፈው የሚሰጡ ብዙዎቹ ፍርደኞች መስቀሉ ጋር ሳይደርሱ ከግርፋቱ የተነሳ ብቻ ሟቾች ናቸው። በመጨረሻም የሚገረፈው ሰው በቃላት ሊገለፅ ከሚችለው በላይ የሆነ ሕመምን በማስተናገድ ወደ ሃይፖቮለሚክ ሁኔታ ይገባል።
ሃይፖ ማለት "ትንሽ" ሲሆን ቮል (ቮልዩም) ማለት "መጠን" ወይም "ይዞታ" ማለት ነው፤ ኢሚክ ማለትም "ደም" ማለት ነው። ስለዚህ የሃይፖቮለሚክ ሁኔታ ብዙ የደም መፍሰስ የገጠመውን ሰው የሚያመላክት ሁኔታ ነው።
ይሄም ሁኔታ አራት ነገሮችን ይፈጥራል።
አንደኛ፦ ብዙ ደም ቢፈስም የደም ዝውውሩን ለማስቀጠል የልብ ምት በፍጥነት እየጨመረ ይሄዳል።
ሁለተኛ፦ የደም ግፊት ይወርዳል። ይህን ተከትሎ ራስን ስቶ መውደቅ ይፈጠራል።
ሶስተኛ፦ ኩላሊቶች የፈሳሽ ማጣራት ስራን መስራት ያቆማሉ። ይህም በብዙ ደም መፍሰስ ምክንያት ብዙ ፈሳሽ ከሰውነት ስለወጣ ተጨማሪ ፈሳሽ እንዳይወጣ ለማድረግ ነው።
አራተኛ፦ ሰውነት በደም መፍሰስ ምክንያት ያጣውን ፈሳሽ ለመተካት ከፍተኛ የሆነ የውሃ ጥማት ይፈጠራል።
ኢየሱስም አንደኛውን የመስቀሉን ክፍል ተሸክሞ ወደ ቀራንዮ በሚወጣበት ጊዜ በሃይፖቮለሚክ ሁኔታ ውስጥ ገብቶ ነበር። በመጨረሻም ኢየሱስ ራሱን ስቶ በመውደቁ የሮማው ወታደር ስምኦንን መስቀሉን እንዲሸከምለት አዘዘው። በኋላ ላይም ኢየሱስ "ተጠማው" ሲል እና ወይን ሲሰጠው እናነባለን።
ግርፋቱ ካደረሰበት ከባድ ጉዳት የተነሳም ኢየሱስ ገና የሚሰቀልባቸው ሚስማሮች በእጆቹ እና በእግሮቹ ከመቸንከራቸው አስቀድሞ እጅግ አሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ ሊሆን እንደሚችል ምንም ጥያቄ የለውም።
ዘ ኬዝ ፎር ክራይስት (The Case for Christ)፥ 1998 እ.አ.አ
ሊ ስትሮቤል ከ ዶ/ር አሌክሳንደር ሜዜሬል ጋር ካደረገው ቃለምልልስ የተወሰደ
ለዚህ ልጥፍ እንዲመች ተደርጎ የተዘጋጀ
ከገፅ 194-196
በጌታ በኢየሱስ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው!!!
✍Kdus zewdu
@cgfsd
ኢየሱስ የተዋረደበት እና የከበረበት ልክ ለማወቅ መንፈስ ቅዱስ በእኛ መካከል የሚኖርበትን አላማ መረዳት አስፈላጊ ነው ። ሰይጣን ወደ ምድር የወረደው በትዕቢቱ ምክኒያት ተጥሎ ሲሆን መንፈስ ቅዱስ ግን ወደ ቤተክርስቲያን የመጣበት ምክኒያት የክርስቶስ መክበር ነበር ። መንፈስ ቅዱስ ወደ ቤተክርስቲያን የወረደበት ልክ ኢየሱስ በሰማያት ያለ ልክ ከፍ ከፍ ያለበት መክበር ነው ። መንፈስ ቅዱስ በቤተክርስቲያን ውስጥ በሀይል ሲንቀሳቀስ ፣ በወንጌል ብዙዎች ሲማረኩ፣ ብዙዎች ከአጋንነት እስራት ነፃ ሲወጡ ፣ በሽተኞች ሲፈወሱ ፣ ቅዱሳን እርስ በእርሳቸው ሲተናነፁ ፣ በህልውና ውስጥ እግዚአብሔርን እየናፈቁ ፣እየፈሩ ፣ በቅድስና መኖርን መንፈስ ቅዱስ በሀይል ሲሰራ የምናስተውለው እውነት ክርስቶስ ምን ያህል በሰማያት በክብር በግርማ እንዳለ ያሳያል ።
#በውስጣችን ያለው መንፈስ ቅዱስ አይቀልብንም ፤ መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥ በመኖሩ በሰማይ ምን እየተከናወለ እንዳለ አውቀናል በዛም ክርስቶስ ከፍ ከፍ ብሎ ያለ ልክ ከብሯል ።
@cgfsd
@ownkin
#በውስጣችን ያለው መንፈስ ቅዱስ አይቀልብንም ፤ መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥ በመኖሩ በሰማይ ምን እየተከናወለ እንዳለ አውቀናል በዛም ክርስቶስ ከፍ ከፍ ብሎ ያለ ልክ ከብሯል ።
@cgfsd
@ownkin
#ፀሎተኛው ኢየሱስ
(ክፍል 2)
ኢየሱስ አስደናቂ የፀሎት ህይወት እንዳለው መፀሀፍ ቅዱሳችን ውስጥ የምናገኘው የተገለጠ እውነት ነው ። ጌታችን ኢየሱስ የፀሎት ህይወት እና ልማዱ ቢያስደንቀንም ከዛ ባልተናነሰ መልኩ የሚፀልይባቸው ጉዳዮችም ያስደንቃሉ ። ኢየሱስ የፀለየባቸው ርዕሶች በራሳቸው ወይ ጉድ የሚያሰኙ ናቸው ። ከመድሃኒታችን የምንማረው የፀሎት ህይወት ብቻ ሳይሆን የምንፀልይበትንም ርዕስ ፣ ሀሳብ ፣ ትኩረት መስጠት ያሉብንም ጉዳዮች ነው ።
በተለይም ደቀመዛሙርቱ ኢየሱስን ፀሎት አስተምረን ሲሉት ያስተማራቸው እንዲህ በማለት ነበር " በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ ስምህ ይቀደስ " የሚል ነበር ። በሰማይ የሚኖረውን አባት ስሙ እንዲቀደስ መፀለይ የኢየሱስ የፀሎት ርዕስ ነበር ። ስምህ ይቀደስ ማለት ስምህ ይለይ ፣ ስምህ ይታወቅ ፣ የስምህ ዝና ይውጣ ፣ በሁሉ ስፍራ አንተ ተወራ፣ ክብር መነጋገሪያ ይሁን እንደማለት ነው ። የኢየሱስ የፀሎት ትኩረት የእግዚአብሔር ክብር እንደነበረ ለደቀመዛሙርቶቹ በትምህርቱ አይተናል ።
ብዙውን ጊዜ ክርስቲያኖች ከምንቸገርባቸው ነገሮች መካከል የመጀመሪያ የምንቆይባቸው የፀሎት የትኩረት ሀሳቦች የሉንም ። እግዚአብሔር በመፀለያችን የሚደሰተውን ያክል በምንፀልይባቸው ጉዳዮችም ይደሰታል ። ከእግዚአብሔር ጋር ያለን እውነተኛ ህብረት መለማመድ ከምንችልባቸው መንገዶች የመጀመሪያን ፀሎት ሲሆን የበለጠ ደግሞ የምንፀልይባቸው ሀሳቦች ከእግዚአብሔር ጋር ምን ያህል ህብረት እንዳለን እንደተረዳን ያሳያሉ ። ኢየሱስ በፀሎቱ የእግዚአብሔር ክብር የስሙ መታወቅ ላይ ትኩረት አደረገ ። በክርስቶስ ያመንን አማኞች እንደመሆናች መጠን የኢየሱስ ትኩረት ያደረገባችው የትኩረት ስፍራዎች ይመለከተናል ። ይባስ ብሎ በውስጣችን የተቀበልነው ቅዱሱ መንፈስ በምን ጉዳይ ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለብን ፣ መቃተት እንደሚኖርብን ፣ ምን የእግዚአብሔር አንገብጋቢ ሀሳብ እንዳለ ያሳስበናል ።
@cgfsd
@ownkin
(ክፍል 2)
ኢየሱስ አስደናቂ የፀሎት ህይወት እንዳለው መፀሀፍ ቅዱሳችን ውስጥ የምናገኘው የተገለጠ እውነት ነው ። ጌታችን ኢየሱስ የፀሎት ህይወት እና ልማዱ ቢያስደንቀንም ከዛ ባልተናነሰ መልኩ የሚፀልይባቸው ጉዳዮችም ያስደንቃሉ ። ኢየሱስ የፀለየባቸው ርዕሶች በራሳቸው ወይ ጉድ የሚያሰኙ ናቸው ። ከመድሃኒታችን የምንማረው የፀሎት ህይወት ብቻ ሳይሆን የምንፀልይበትንም ርዕስ ፣ ሀሳብ ፣ ትኩረት መስጠት ያሉብንም ጉዳዮች ነው ።
በተለይም ደቀመዛሙርቱ ኢየሱስን ፀሎት አስተምረን ሲሉት ያስተማራቸው እንዲህ በማለት ነበር " በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ ስምህ ይቀደስ " የሚል ነበር ። በሰማይ የሚኖረውን አባት ስሙ እንዲቀደስ መፀለይ የኢየሱስ የፀሎት ርዕስ ነበር ። ስምህ ይቀደስ ማለት ስምህ ይለይ ፣ ስምህ ይታወቅ ፣ የስምህ ዝና ይውጣ ፣ በሁሉ ስፍራ አንተ ተወራ፣ ክብር መነጋገሪያ ይሁን እንደማለት ነው ። የኢየሱስ የፀሎት ትኩረት የእግዚአብሔር ክብር እንደነበረ ለደቀመዛሙርቶቹ በትምህርቱ አይተናል ።
ብዙውን ጊዜ ክርስቲያኖች ከምንቸገርባቸው ነገሮች መካከል የመጀመሪያ የምንቆይባቸው የፀሎት የትኩረት ሀሳቦች የሉንም ። እግዚአብሔር በመፀለያችን የሚደሰተውን ያክል በምንፀልይባቸው ጉዳዮችም ይደሰታል ። ከእግዚአብሔር ጋር ያለን እውነተኛ ህብረት መለማመድ ከምንችልባቸው መንገዶች የመጀመሪያን ፀሎት ሲሆን የበለጠ ደግሞ የምንፀልይባቸው ሀሳቦች ከእግዚአብሔር ጋር ምን ያህል ህብረት እንዳለን እንደተረዳን ያሳያሉ ። ኢየሱስ በፀሎቱ የእግዚአብሔር ክብር የስሙ መታወቅ ላይ ትኩረት አደረገ ። በክርስቶስ ያመንን አማኞች እንደመሆናች መጠን የኢየሱስ ትኩረት ያደረገባችው የትኩረት ስፍራዎች ይመለከተናል ። ይባስ ብሎ በውስጣችን የተቀበልነው ቅዱሱ መንፈስ በምን ጉዳይ ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለብን ፣ መቃተት እንደሚኖርብን ፣ ምን የእግዚአብሔር አንገብጋቢ ሀሳብ እንዳለ ያሳስበናል ።
@cgfsd
@ownkin
መውደዱ በሥጋው መቈረስ ደመቀ፤ ለእኛ ያለው ፍቅሩ በደሙ መፍሰስ ታተመ። በቍስሉ ውስጥ ከእግዚአብሔር ጋር ተጨባበጥን። በሰማይ ለእግዚአብሔር ክብር፥ በምድር ለሰው ልጅ ሥምረት ኾነ (ሉቃ. 2፥14)። እነሆ፥ ዐዲስ የወዳጅነት መንገድ ተከፈተ። ከእግዚአብሔርም ጋር ኾነ ከሰው ጋር እንታረቅ ዘንድ መድኀኒት በቀራንዮ ተቈረሰ። ድኅነት ታወጀ። ኀጢአት ተሰረየ፤ የቀደመች ኀጢአት በእግዚአብሔር ችሎታ ተተወች፤ ዐመፃ ተጨረሰ፤ የዘላለም ጽድቅ ገባ፤ ምሕረት ተበሠረ፤ ፍቅር በመስቀል ላይ ሠመረ። በትንሣኤው ኀይል ጨለማ ድል ተነሣ፤ ለእግዚአብሔር ክብር ለሰውም ሰላም ኾነ።
ሰሎሞን አበበ ገብመድኅን
@cgfsd
@ownkin
ሰሎሞን አበበ ገብመድኅን
@cgfsd
@ownkin
በመፀሀፍ ቅዱስ ውስጥ የጠፋውን ልጅ ታሪክ ስናነብ በጣም የሚደንቀን የጠፋውን ልጅ በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው የአባቱ ልብ ነው ። የአባትነትን ልብ ያየንበት ግሩም ታሪክ ነው ። ነገር ግን አባትዬው እጅግ ደስ የሚለው ጉዳይ ቤት ያለው ያልጠፋው ልጅ አለመጥፋት ብቻ ሳይሆን የጠፋውን ልጅን ያልጠፋው ልጅ አፈላልጎ እንዲያገኝ እና ወደ አባቱ ቤት እንዲመለስ አባቱ በብርቱ ይፈልጋል ። ቤት ያለው ልጅ የአባቱን ልብ አላገኘም ነበር ፤ ቤት ተቀምጦ ከአባቱ ልብ ርቋል ። ኢየሱስ ግን ከዙፋን ፣ ከሰማይ ድረስ የአባቱን ልብ ተረድቶ በበረት ተኝቶ ፣ በሰው መንደር አድጎ ፣ በመስቀል ላይ ውሎ ፣ በመቃብር ውስጥ አድሮ የጠፋውን የሰው ልጅ ፈልጎ አፈላልጎ አገኘ ። የአባት ልብ መረዳት እንዴት ደስ ይላል !! በኢየሱስ በኩል የተገለጠ የአብ ልብ አለ ። የአብን የልብ ሀሳብ ለመረዳት የፈለገ ማንም ቢኖር የአብን ልብ ባረካው በኢየሱስ በኩል ይገኛል ። አብ በልጁ ኢየሱስ የልቡ ስለደረሰ እሱን ስሙት ብሎ የልብ የልቡን በኢየሱስ በኩል ተናግሯል ።
@cgfsd
@ownkin
@cgfsd
@ownkin