በክርስቶስ ( in christ)
697 subscribers
98 photos
34 videos
41 files
37 links
Who is ownership of kingdom
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin
Download Telegram
አለም ከተፈጠረ ጀምር እሰከ ዛሬ ድረስ ያልተለወጡ የምንጊዜም የመጨረሻ እጅግ በጣም ድንቃድንቅ እና ትላልቅ ሶስት ተአምራት (the greatest miracle ever)

#የክርስቶስ ሰው መሆን
#የክርስቶስ መሞት
#የክርስቶስ ትንሳኤ

ምን አይነት ተአምር ነው !!
(what a miracle)

@cgfsd
@ownkin
#የክርስቶስ_ግርፋት
#በምሁሩ_ዕይታ
#ክፍል_1

የወዙ እንደ ደም ነጠብጣብ መሆን፥ ይሄ ሁኔታ በህክምናው ዓለም ሄማትድራሲስ በመባል ይታወቃል። ብዙም የተለመደ አይደለም፤ ነገር ግን ከፍተኛ ከሆነ ሥነልቦናዊ ጫና ጋር የሚያያዝ ሁኔታ ነው።

ከባድ ወይም ከመጠን ያለፈ ጭንቀት ላብ እንዲመነጭ በሚያደርጉ እጢዎች ውስጥ የሚገኙትን ደም ስሮች የሚጎዱ ኬሚካሎች እንዲረጩ ያደርጋል። በዚህም በእነዚህ እጢዎች ውስጥ ጥቂት የደም መፍሰስ ይፈጠራል። ስለዚህ ከሰውነት የሚወጣው ላብ ከደም ጋር የተዋሃደ ይሆናል። ይህም ሲሆን ብዙ የደም መፍሰስ ይኖራል ማለት አይደለም፤ ነገር ግን ጥቂት ደም ከላብ ተቀላቅሎ ይገኛል።

ይህ ክስተት የሰውነት ቆዳን ስስና ደካማ ያደርገዋል፤ ኢየሱስም በቀጣዩ ቀን በሮማውያን ሲገረፍ የሰውነቱ ቆዳ እጅግ ደካማ ሆኖ ነበር። የሮማውያን ግርፊያ እጅግ ጭካኔ የተሞላበት እንደሆነ ይታወቃል። ተለምዷዊው ግርፋት 39 ግርፋት ያህል ነው። ብዙውን ጊዜ ግን ከዚህም ሊበልጥ ይችላል፤ በተለይም ደግሞ ገራፊው ወታደር እንዳለበት ሙድ ወይም ስሜት ሊለዋወጥ ይችላል።

አንድ የሮማ ወታደር ለግርፊያ የሚጠቀመው ጅራፍ ከቆዳ የተሰፋ እና ትንንሽ የማይባሉ የብረት ኳሶች የታሰረበት ጅራፍ ነው። አንዱ ግርፋት ሰውነት ላይ ሲያርፍ እነዚህ የብረት ኳሶች ጥልቅ ቁስል እና ጉዳት ያመጣሉ፤ በኋላም ግርፋቱ ሲደጋገም ከቁስለት ያልፍና የሰውነት ቆዳ እየተከፈ ይሄዳል። ጅራፉ የአጥንት ስብርባሪዎች ጭምር አብሮ የተሰፋበት ሲሆን፥ በሚዘገንን ሁኔታ የሰውነትን ቆዳ ይጎዳሉ።

ይህ ግርፋት የሚደርስበት ሰው ጀርባ፥ ግርፋቱን ተከትሎ ከሚፈጠሩት ትልልቅ ክፍተቶች የተነሳ ሊቦጫጨቅ የሚችል በመሆኑ የጀርባ አጥንት የተወሰነው ክፍል ሳይቀር ሊታይ የሚችልበት አጋጣሚ ይፈጠራል። ግርፋቱ ከትከሻ አንስቶ እስከ ታችኛው ጀርባ፥ አልፎም መቀመጫን እና የእግር ታፋ ጀርባን ሳያስቀር ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል። እጅግ አሰቃቂ ነው።

የሮማውያንንን ግርፍያ ያጠና አንድ ፊሲሺያን "ግርፋቱ እየቀጠለ ሲሄድ፥የቁስሎቹ መቀደድ ወደታችኛው የአጥንት ጡንቻ ድረስ በመዝለቅ እንደደም የሚፈስ የተቦጫጨቀ ሥጋን ይፈጥራል።

ዩሴቢየስ የተባለ በሶስተኛው ክፍለዘመን የነበረ አንድ የታሪክ ምሁር የግርፋቱን ሁኔታ ሲያስረዳ "ይህ መከራ የሚደርስበት ሰው ደም ሥሮቹ፥ ጡንቻዎቹ፥ ጅማቶቹ እና አንጀቱ ሳይቀር ከግርፋቱ የተነሳ ለዕይታ ተጋላጭ ይሆናሉ።

ተገርፈው እንዲሰቀሉ ታልፈው የሚሰጡ ብዙዎቹ ፍርደኞች መስቀሉ ጋር ሳይደርሱ ከግርፋቱ የተነሳ ብቻ ሟቾች ናቸው። በመጨረሻም የሚገረፈው ሰው በቃላት ሊገለፅ ከሚችለው በላይ የሆነ ሕመምን በማስተናገድ ወደ ሃይፖቮለሚክ ሁኔታ ይገባል።

ሃይፖ ማለት "ትንሽ" ሲሆን ቮል (ቮልዩም) ማለት "መጠን" ወይም "ይዞታ" ማለት ነው፤ ኢሚክ ማለትም "ደም" ማለት ነው። ስለዚህ የሃይፖቮለሚክ ሁኔታ ብዙ የደም መፍሰስ የገጠመውን ሰው የሚያመላክት ሁኔታ ነው።

ይሄም ሁኔታ አራት ነገሮችን ይፈጥራል።
አንደኛ፦ ብዙ ደም ቢፈስም የደም ዝውውሩን ለማስቀጠል የልብ ምት በፍጥነት እየጨመረ ይሄዳል።
ሁለተኛ፦ የደም ግፊት ይወርዳል። ይህን ተከትሎ ራስን ስቶ መውደቅ ይፈጠራል።
ሶስተኛ፦ ኩላሊቶች የፈሳሽ ማጣራት ስራን መስራት ያቆማሉ። ይህም በብዙ ደም መፍሰስ ምክንያት ብዙ ፈሳሽ ከሰውነት ስለወጣ ተጨማሪ ፈሳሽ እንዳይወጣ ለማድረግ ነው።
አራተኛ፦ ሰውነት በደም መፍሰስ ምክንያት ያጣውን ፈሳሽ ለመተካት ከፍተኛ የሆነ የውሃ ጥማት ይፈጠራል።

ኢየሱስም አንደኛውን የመስቀሉን ክፍል ተሸክሞ ወደ ቀራንዮ በሚወጣበት ጊዜ በሃይፖቮለሚክ ሁኔታ ውስጥ ገብቶ ነበር። በመጨረሻም ኢየሱስ ራሱን ስቶ በመውደቁ የሮማው ወታደር ስምኦንን መስቀሉን እንዲሸከምለት አዘዘው። በኋላ ላይም ኢየሱስ "ተጠማው" ሲል እና ወይን ሲሰጠው እናነባለን።

ግርፋቱ ካደረሰበት ከባድ ጉዳት የተነሳም ኢየሱስ ገና የሚሰቀልባቸው ሚስማሮች በእጆቹ እና በእግሮቹ ከመቸንከራቸው አስቀድሞ እጅግ አሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ ሊሆን እንደሚችል ምንም ጥያቄ የለውም።

ዘ ኬዝ ፎር ክራይስት (The Case for Christ)፥ 1998 እ.አ.አ
ሊ ስትሮቤል ከ ዶ/ር አሌክሳንደር ሜዜሬል ጋር ካደረገው ቃለምልልስ የተወሰደ
ለዚህ ልጥፍ እንዲመች ተደርጎ የተዘጋጀ
ከገፅ 194-196

በጌታ በኢየሱስ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው!!!

Kdus zewdu

@cgfsd
ሰላም የበክርስቶስ ቤተሰቦች ለሚመጡት ተከታታይ ጊዜያት #የክርስቶስ የመስቀል ስራ በሚል ሀሳብ ከተለያዩ አገልጋዩች ጋር በየ ሳምንቱ በተከታታይ በዚሁ ሀሳብ እንማራለን ።


@cgfsd
@ownkin