ጉራማይሌ Delivery 🇪🇹
15.5K subscribers
616 photos
41 videos
1 file
79 links
ምንም አይነት መፅሀፍ ይዘዙን ያሉበት ቦታ ድረስ በነፃ እናመጣሎታለን፡
በሚያስገርም "ከ10-50%" በሆነ የዋጋ ቅናሽ ሞክረው ይዩን በአገልግሎታችን ይደሰታሉ

Free delivery
@Guramaylebooks

@Guramayelie 0912319263
Download Telegram
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያንን ከኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያን ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነጥሎ ማየት ይከብዳል፡፡ ቤተክስርቲያኒቱ ለኢትዮጵያ ህልውና ዋጋ ብትከፍልም ለውለታዋ ጥርስ እንዲነከስባት ሆናለች፡፡
ለመሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክስርቲያን በምን ምክንያት ጥርስ ተነከሰባት? ውለታዋና በደሏስ ምንድነው?
እስልምና፣ ወንጌላውያን እና ካቶሊክ ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጋር የነበራቸው ሙግት በአስደናቂ ሁኔታ በመጽሐፉ ውስጥ ተዳስሷል፡፡ በሙግቱ ማን ረትቶ ይሆን?
ላሊበላ ሶስት ቀናት ሞቶ የተገለጠለት አስገራሚ ሚስጥርም ተካትቶበታል፡፡ ብዙም ያልተነገረለት ላሊበላ ሞቶ የተገለጠለት ምስጢር ምን ይሆን?
ታቦተ ፂዮንን በአይናቸው ያዩት አጼ ኢያሱን ጨምሮ የጥቂት ሰዎች ምስክርነት በሚገርም ሁኔታ በመጽሐፉ ላይ ሰፍሯል፡፡ ታቦተ ፂዮንን በአይናቸው ያዩ ሰዎች ምን ተናረው ይሆን?
ኦርቶጵያ መጽሐፍ የሚነግረን ብዙ አስገራሚ ታሪኮች አሉ፡፡


ኦርቶጵያ ትርጉም ራሴላስ ጋሻነህ
የገፅ ብዛት - 352 የተለጠፈበት ዋጋ - 350 ብር
መሸጫ ዋጋ - 220 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263
ስለሃገሩ ተናግሮ አይጠግብም ሃገር በቀል እውቀቶች ላይ ብዙ ለፍቷል ኢትዮጵያዊነት በደምስሩ ውስጥ ገብቷል። ይጠቅማል ያላቸውን እውቀቶች፣ኢትዮጵያዊ ፍልስፍናዎች ሳይደክም ለትውልዱ ዘርቷል አሁንም እየዘራ ይገኛል።በሃይማኖቱ ድርድር አያውቅም ሃሰተኞችና አላዋቂዎችን ይሞግታል ።ዘረኞች እጅግ አብዝተው ይጠሉታል ። ኢትዮጵያዊነት ላይ ያጠነጠኑ በዙ አጫጭር ስልጠናዎችን ሰጥቷል።ላመነበት ጉዳይ ወደ ኋላ አያውቅም።
መምህር ፋንታሁን ዋቄ ።
አሁን ላይ ያየውን የምእራቡን እሳቤ ከተለያዩ እይታ አንጻር አይቶ በመጽሐፍ መልክ ይዞልን ብቅ ብሏል ።
"ሥዝም ሰብዊነት /secular humanism / የልማታዊ ወንጀሎች ምንጭ" ።
ይህ መጽሐፍ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ቢያነበው ያተርፍበታል። ተጽሐፈ ዲበኩሉ።


ሥዝም ሰብአዊነት ፋንታሁን ዋቄ
የገፅ ብዛት - 471 የተለጠፈበት ዋጋ - 390 ብር
መሸጫ ዋጋ - 350 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263
ሙሉ በሙሉ እውነተኛ ታሪክ
የሞት ፍርድ የተፈረደባት አንዲት እንስት ይቅርታ ጠይቂና የሞት ፍርዱ ይነሳልሽ ብትባል እንቢ አሻፈረኝ ትላለች፡፡
ምሕረትን እንዳትቀበል ያደረጋት፣ ሕይወቷን ያስመረረውና የሞት ጽዋውን ያሰኛት ምክንያት ምን ይሆን?
ከእስር ቤት የምትወጪበት አንድ ተስፋ ተገኝቷል፡፡ ለፕሬዚዳንቱ የይቅርታ መልዕክት ፅፈሽ ይቅርታ እንዲደረግልሽና ሁለተኛ ወንጀል ላለመስራት ቃል የምትገቢ ከሆነ ከእስር ቤት እንደምትወጪ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡”
“ይቅርታ እኔ ነፃ መሆን አልፈልግም፡፡ ለሰራሁት ወንጀል ደግሞ ይቅርታ መጠየቅ አልፈልግም፡፡ በዚያ ላይ እናንተ ወንጀል ብላችሁ የምትጠሩት ወንጀል አይደለም” አልኩት፡፡ “ከዚህ ወጥቼ አንተ እንደምትለው እንደገና መኖር ብጀምር መግደሌን አላቆምም፡፡ ስለዚህ የይቅርታ ደብዳቤ ለፕሬዚዳንቱ መላክ አያስፈልግም፡፡ እኔ በመኖርም፣ በመሞት… በሁለቱም አሸናፊ ነኝ፡፡”


ማራ ትርጉም መላኩ ዓለም
የገፅ ብዛት - 206 የተለጠፈበት ዋጋ - 250 ብር
መሸጫ ዋጋ - 170 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263
"ጎሹ አረጀና ልቡ ቢዘናጋ
ጉራምባ ወረደ አንበሳን ሊወጋ
ጎሹ እስከነልጁ ጉራምባ ላይ ወርዶ
ያንበሳውን ፊት ቢያይ ወደቀ ተዋርዶ።"

ደጃዝማች ካሳ ኃይሉ ‹‹ዳግማዊ ቴዎድሮስ ንጉሰ ነገሥት ዘኢትዮጵያ›› ተብለው ከመንገሳቸው በፊት ከግዛት ባላባቶች ጋር ካደረጓቸው ታላላቅ ጦርነቶች መካከል አንዱ የነበረው ኅዳር 19 ቀን 1845 ዓ.ም ጉር አምባ ላይ የተካሄደውን የጉራምባ ጦርነት ላይ ደጃዝማች ጎሹ ዘውዱን ከሸነፉ በኋላ የተገጠመላቸው ግጥም ነው።
ደጃዝማች ጎሹ ዘውዴ የራስ ኃይሉ ዮሴዴቅ የልጅ ልጅ (የወይዘሮ ድንቅነሽ ኃይሉ ልጅ) እንዲሁም የዳሞቱ ባላባት የደጃዝማች ዘውዴ ልጅ ናቸው፡፡ ልጃቸው ደጃዝማች ብሩ ጎሹ ከአባቱ ጋር ሆኖ ጉር አምባ ላይ ከደጃዝማች ካሣ ጋር እየተዋጋ ሳለ፣ አባቱ ደጃዝማች ጎሹ መመታታቸውን ሲያይ ሸሽቶ ዳሞት ገብቶ ነበር፡፡ በኋላም ተይዞ ድንጋይ ተሸክሞ ደጃዝማች ካሣን ምህረት ጠይቋል፡፡ ከመጽሐፉ የተወሰደ።


ዐፄ ቴዎድሮስ እና የኢትዮጵያ አንድነት
ከተክለ ጻድቅ መኲሪያ
የገፅ ብዛት - 514 የተለጠፈበት ዋጋ - 456 ብር
መሸጫ ዋጋ - 410 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263
ለእስልምና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የኢድ-አል አድሃ በዓል እንዲሆንላችሁ እንመኛለን ።
ሚካኤል አስጨናቂ የጻፋቸውን ወጎችና አጫጭር ታሪኮች ለኅትመት ከመብቃታቸው አስቀድሞ አነባቸው ዘንድ ያቀረበውን ግብዣ በአክብሮት ተቀብዬ ተመልክቻቸው ነበር።
ምስክር ለመቆም በቂ ይመስሉኛል።
እጅግ መልካም የሆነ የማስታወስና የመተረክ ብቃት ያለው ማዕከላዊ ጸሐፊ (ደራሲ) ሆኖ አግኝቼዋለሁ መጽሐፉን የሚያነቡም ቢያተርፉ እንጂ እንደማይከስሩ ስምዐ - ጽድቄን አስቀምጫለሁ።
በእርግጠኝነት ተወዳጅ መጽሐፍ ለመሆን የሚቻለው ሥራ ነው። "ሸግዬ ሸጊቱ" !።!
ገጣሚ፣ ደራሲ እና ባለቅኔ ኤፍሬም ሥዩም ስለመጽሐፉ የሰጠው አስተያየት።


ሸግዬ ሸጊቱ ሚካኤል አስጨናቂ
የገፅ ብዛት - 292 የተለጠፈበት ዋጋ - 350 ብር
መሸጫ ዋጋ - 260 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263
የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ይኹኖ አምላክ እስከ ዓፄ ሱስንዮስ ከ1270 - 1632 ዓ.ም

ይህ መጽሐፍ የመካከለኛውን ዘመን የኢትዮጵያ ታሪክ በጥሩ አተያይ የሚያትት አዲስ መጽሐፍ ሲኾን የሰለሞናዊውን ሥርወ መንግሥት ከአነሳሱ እስከ ውድቀቱ እና በወይ ባህር ክልል የነበረውን የሙስሊሙንና የአውሮፓውያንን ፉክክር የሚዳስስ በእስታኤላዊው ፕሮፌሰር ሞርድኃይ አቢር የተፃፈ ሲሆን በበሳል የአተረጓጎም ብቃት በማውሮ አዛሪዮስ ተተርጉሞ ለንባብ በቅቷል።

መጽሐፉ አስቸጋሪውንና ውስብስቡን የመካከለኛውን ዘመን የሚተነትንንና የዘመኑን የታሪክ ክፍተት የሚሞላ እንዲሁም የእስልምና ኃይሎች መነሳትን የኦሮሞን መስፋፋት ፣ የሰለሞናዊው መንግስት የውድቀት ምክንያቶች፣ በቀይ ባህር ዳርቻ የነበሩት የትግራይ ሹማምንቶች የአውሮፓውያንን ሽርክና በተጓዥነት ስም የሚመጡ አውሮፓውያን ስውር ፍላጎት ጭምር ተተንትኖበታል።


የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ይኹኖ አምላክ እስከ ዓፄ ሱስንዮስ ከ1270 - 1632 ዓ.ም ተርጓሚ ማውሮ አዛሪዮስ
የገፅ ብዛት - 314 የተለጠፈበት ዋጋ - 380 ብር
መሸጫ ዋጋ - 250 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263
የኢህአዴግ የማጥቃት ጦርነት በምዕራብ አምቦን አልፎ በሰሜን ዓባይን ተሻግሮ በምሥራቅ ደብረብርሃንን ተቆጣጥሮ በሁሉም አቅጣጫ ወደ ዋና ከተማይቱ እየቀረበ በሄደ ጊዜ ከፕሬዚዳንት መንግሥቱ ህዝብ የሚጠብቀው ነገር ነበር። ቢያንስ ቤተ መንግሥት ዙሪያ በታማኝነት የሚጠብቃቸውን ልዩ ብርጌድ ይዘው እስከመጨረሻው ይፋለማሉ አለበለዚያም የሶማሊያው መሪ ዚያድ ባሬ እንዳደረገው ታማኙን ጦራቸውን ይዘው ወደ አንድ አቅጣጫ ይወጣሉ ተከታይም ካገኙ ተጠናክረው ውጊያውን ይቀጥላሉ የሚል ነው። በብሔራዊ ሸንጎ አራተኛ ጉባኤ ወቅት የስብሰባው ተካፋይ የነበሩ አንድ ጳጳስ "ክቡር ፕሬዚዳንት ሁሌም ስለዚህች አገር ተንገብግበው ሲናገሩ እሰማለሁ፤ ዛሬም ብዙ ነገር ተናግረዋል፤ ህዝቡም ከጎንዎ እንደሚሆን አምናለሁ። ኢትዮጵያ የመበታተን አደጋ አንዣቦባታል። እስከመጨረሻው ሞተን ልናድናት ይገባል። ያለፉት የኢትዮጵያ መሪዎች ብዙዎቹ ጥሩ ታሪክ አላቸው። አፄ ቴዎድሮስ እጃቸውን ለጠላት ላለመስጠት ሽጉጣቸውን ጠጥተው አልፈዋል። ከእርስዎም የምንጠብቀው ይኼንኑ ነው። ብዙ ሃሜት ይሰማል አገር ጥለው ሊሄዱ ነው እያለ ሰው ያወራል። እኔ ግን እልዎታለሁ ! እዚህቹ የተቀመጡበት ወንበር ላይ ደርቀው መቅረት አለብዎት እንጂ ህዝቡን ትተው እንዳይሸሹ " ብለው ስጋታቸውን ገልጸው ነበር።

ትውልድ ያናወጠ ጦርነት ክፍል ፩ ሻለቃ ንጋቱ ቦጋለ
የገፅ ብዛት - 354 የተለጠፈበት ዋጋ - 355 ብር
መሸጫ ዋጋ - 260 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263
ትውልድ ያናወጠ ጦርነት ክፍል ፪ ሻለቃ ንጋቱ ቦጋለ
የገፅ ብዛት - 334 የተለጠፈበት ዋጋ - 355 ብር
መሸጫ ዋጋ - 260 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263
#የፍልስፍና_ሀሁ
እና
#ፍልስፍና_ከዘርዓ_ያዕቆብ_እስከ_ሶቅራጥስ

#እውነት_ምንድን_ነው? የሚለው ጥያቄ የምንጊዜም እንቆቅልሽ ጥያቄ ሆኖ ኖሯል፡፡ ከግሪክ እስከ ሮም፣ ከህንድ እስከ ጃፓን፣ ከአውሮፓ እስከ አሜሪካ ድረስ በተለያዩ ዘመናት የኖሩ አያሌ ፈላስፎች ይህን ጥያቄ ለመመለስ እድሜያቸውን ሰውተዋል፡፡

ከሰዎች ተለይተው በየዋሻውና በየምኩራቡ እውቀትን ክፉኛ ቢሹም፣ እስካሁን ሁሉንም የሚያስማማ መልስ ሊገኝ አልቻለም፡፡ ይሁንና የሁሉም መልስ ደግሞ ስህተት ነው ለማለት አይቻልም፡፡ ሁሉም የየራሱ እውነት አለውና፡፡ ፍለጋው አሁንም ቀጥሏል፡፡ ሁለቱም መጽሐፍት #የፍልስፍና_ሀሁ እና #ፍልስፍና_ከዘርዓ_ያዕቆብ_እስከ_ሶቅራጥስ ደግሞ አብረውን እውነትን ይፈልጋሉ፡፡

ፍጥረትና ህይወት ከየት ተገኘ?
የምንኖረው ለምንድን ነው?
የህይወት የመጨረሻው አላማ ምንድን ነው?
ለምን ወደዚህ ምድር መጣን?
ወዴትስ እንሄዳለን?

እነዚህና ሌሎች አያሌ ጥያቄዎች የእውነትን እውነተኛ መልስ ይጠብቃሉ፡፡ ዴስካሬት በፕላቶ መልስ ቢስቅም፣ ሩሶ በስፒኖዛ ፍልስፍና ቢበሳጭም፣ ፓይታጎራውያን በኢፒስኩሮሶች ቢያፌዙም፣ ሁሉም ግን በአንድ ነገር ብቻ ፈጽሞ ይስማማሉ፡፡

#የመጨረሻው_የጥበብ_ፍለጋ ፍልስፍና መሆኑን፡፡

#የፍልስፍና_ሀሁ እና #ፍልስፍና_ከዘርዓ_ያዕቆብ_እስከ_ሶቅራጥስ መጽሐፍት ስለ ፍልስፍና አስደናቂና አዝናኝ ጉዞ ይተርካሉ፡፡

ከአቴንስ እስከ ኤፌሶን፣ ከለንደን እስከ ፓሪስ፣ ከንጉስ እስከ ባሪያ በተለያየ ዘመን የኖሩ አለምን የቀየሩ ፈላስፎችን በር ያንኳኳሉ፡፡ መሰረታዊ ፍልስፍናን ማወቅ አለብኝ ለሚልና የኢትዮጵያንና የአለምን ፍልስፍናን ለተጠማ አንባቢ እነዚህ መጽሐፍት ትልቅ ገጸ በረከቶች ናቸው፡፡

ፍልስፍና ከዘርዓ ያዕቆብ እስከ ሶቅራጥስ 220 ብር
የፍልስፍና ሀሁ 220 ብር
ይህ መጽሐፍ የታላቁ ንጉሰ ነገስት የግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ እና የኢትዮጵያን ታሪክ የያዘ ትልቅ ቅርስ ነው። መጽሐፉ በውስጡ የያዛቸው እጅግ በርካታ የኢትዮጵያ ታሪክ ውጣ ውረዶች አሉት። በዚያ አባጣ ጎርባጣ በበዛበት ጉዞ ውስጥ ጃንሆይ ከልጅነት ዘመናቸው ጀምሮ እስከ ስደታቸው ያለው ታሪክ በውብ የአፃፃፍ ቴክኒክ ተደራጅቶ እነሆ ለዳግም ንባብ በቅቷል።
በዚህ መፅሐፍ ውስጥ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ፀንታ እንድትቆም ልጆችዋ እና ንጉሰ ነገስትዋ የተጓዙበትን ረጅም መንገድ እና የከፈሉትን መስዋዕትነት የሚዘክር የአንድ ታላቅ ንጉስን ብዕር እናነባለን። ድንቅ መጽሐፍ ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊያነበው እና በቤቱ የመጽሐፍት መደርደሪያ ላይ ሊኖሩት የሚገባ ነው። ጋዜጠኛ እና አርታኢ ጥበቡ በለጠ ስለመጽሐፉ የሰጠው አስተያየት።


ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ
ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ
የገፅ ብዛት - 284 የተለጠፈበት ዋጋ - 460 ብር
መሸጫ ዋጋ - 390 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263
Audio
"ኢትዮጵያዊነት"
ከአንዷለም ቡኬቶ የማህበራዊ ገጽ የተወሰደ።
በዚህ አስከፊ ጊዜ የሀገራችንን ስም በጥሩ ላስነሱ አትሌቶቻችን ክብር ይገባቸዋል። 💚💛❤️
እንኳን በሰላም ለሀገራችሁ አበቃችሁ። 🙏🙏🙏
ሄኖክ ስዩም በሀገራችን ጉዞና ጉብኝት የቱሪዝም ዘርፍ የተሰማራ ጋዜጠኛ ነው። ተጓዡ ጋዜጠኛ በሚል ቅፅል ስሙ ይታወቃል።
የጉዞ ማስታወሻዎችንም በመጻፍ ለሕትመት አብቅቷል ፤ ከዚህ ቀደም "የመንገድ በረከት" ፣ "ጎንደርን ፍለጋ" እና "ሀገሬን" የተባሉ ሦስት መጻሕፍትን ለተደራሲያን አቀቧል። "ደቦ" እና "አቦል" በተሰኙ የጋራ ስብስብ ስራዎችም የጉዞ ማስታወሻ ሥራዎቹን አሳትሟል። ይህ "ወደ ኢትዮጵያ ሰዎች" የተባለ ስራው ለሀገሩ ሰው የላካቸውን መልእክቶች የያዘ አዲስ አቀራረብ ነው።


ወደ ኢትዮጵያ ሰዎች
ሄኖክ ስዩም (ተጓዡ ጋዜጠኛ)
የገፅ ብዛት - 186 የተለጠፈበት ዋጋ - 250 ብር
መሸጫ ዋጋ - 190 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263
ንግግር ለመጀመር አትጣደፍ። ጥድፊያ መሸበርንና ሁኔታዎችን መቆጣጠር አለመቻልን ያሳያል።
ድሉ ያለው ፍርሀት አልባ በሆነው የአእምሮ መዋቅር ውስጥ ነው። ፕሮፌሰር ዎልተር ዲል ስኮት "በቢዝነስ ውስጥ ስኬት እና ውድቀት የሚመጣው ከአእምሯዊ አቅም ይልቅ በአእምሯዊ አመለካከት ነው" ሲል ይናገራል። የፍርሃት አመለካከትን አስወግዱ። እናም ይህንን ከፍርሃት የነጻ አመለካከት ማግኛ ብቸኛው መንገድ ደግሞ አመለካከቱን ማግኘት ብቻ እንደሆነ አስታውሱ።
በእርጋታ ከልብ ተንፍሱ ፤ ንግግራችሁን ልክ ለአንድ ትልቅ ጓደኛችሁ እያወራችሁ እንደሆናችሁ በተረጋጋ የወግ ድምጽ ጀምሩ። ንግግራችሁንም እንደፈራችሁት መጥፎ ሆኖ አታገኙትም። ይህ ልክ ውሃ ውስጥ ጠልቆ እንደመግባት ዓይነት ነገር ነው። ውሃው ውስጥ ጠልቃችሁ ከገባችሁ በኋላ ውሃው ይረጋጋል። ስለ እውነቱ ከሆነም ለጥቂት ጊዜ ንግግሮችን ካደረጋችሁ በኋላ የውሃ ጠለቃውን በደስታ የምትጠብቁ ይሆናል። ከታዳሚው ፊት ቆማችሁ ታዳሚውን ሃሳቦቻችሁ ደስታን የሚያጭሩላችሁ መሆኑን ታዳሚው ያስብ ዘንዳ ታደርጋላችሁ።


የንግግር ጥበብ. ዴል ካርኔጊ
የገፅ ብዛት - 212 የተለጠፈበት ዋጋ - 250 ብር
መሸጫ ዋጋ - 200 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263
... አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
"መንፈሳችንን ነፃ ስለ ማውጣት"

በአንተ ውስጥ መልካም ነገርን ብታገኝ እንኳ በዚህ ነገር አትታበይ ወይንም አትመካ።

በራስህ ጽድቅ ራስህን አትዋጋ፤ ነገር ግን ክብርህን ሁሉ ለእግዚአብሔር ስጥ። ለእናንተ የሚገባው ለእርሱ አይደለም፤ እርሱ ቸር ነውና መልካሙን ሁሉ ፈጣሪ እንደኾነ ደግ ነገር በእርሱ ነውና። እሱ እራሱ ጥሩ ነው። ስለሆነም ጥሩነት በራሱ ያለ እርሱ ምንም ማድርግ አይችልም። ስለዚህ የእግዚአብሔርን ክብር ዘርፈህ ለራስህ አትስጠው። እርግጥ ነው፤ ልክ እንደ ጨረቃ ልታበሩ ብትችሉ እና ሙሉ ጨረቃ እስክትሆኑ ድረስ ብርሀናችሁ ቢጨምርም፣ በነገሩችሁ ሁሉ ውስጥ ጨረቃ ብርሀኗን ከፀሐይ የምታገኝ (የፀሐይን ብርሀን የምታንፀባርቅ) የራሷ የብርሀን ምንጭ የሌላት ግዑዝ መሆኗን ልብ አድርግ። ስለዚህ ፀሐይ ከሌሎች ጨረቃ በባህሪዋ ጨለማ ስለሆነች ልናያት ሁሉ አንችልም። አሁን ጨረቃ በፀሐይ ፊት ስለብርሀኗ ለመናገር ትደፍራለችን?!


መንፈሳችንን ነጻ ስለማውጣት
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
የገፅ ብዛት - 166 የተለጠፈበት ዋጋ - 250 ብር
መሸጫ ዋጋ - 190 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263
የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ አራት አዳዲስ መጽሐፍት በአንድ ላይ የታተሙበት!

የደስታ ቀናት እንደ ሰማይ ሲርቁ…
ክፉ ቀናት እንደ አጀብ ሲከቡን…
ሞት አንድ አማራጭ ሆኖ ሲቀርብ…
ውስጣዊ ሰላማችን ሲረበሽ…
እርጋታ ፈጽሞ ሲጠፋ….

…ያን ጊዜ “ጌታ ሆይ እስከመቼ?” እንላለን፡፡ ደግሞም በልጅነት ሰቆቃ በአባቶቻችን አንደበት
#እስከማዕዜኑ? እንላለን፡፡

“እንደ ልጄ እንደ ዳዊት ቀና ሁን፣ እንደ ታላቁ ታጋሽ እንደ ኢዮብ ሁንልኝ፣ የቀጠርኩልህ ቀን ሲደርስ የመከራህን ቀናት አስረሳሃለሁ! እንደ ተወዳጁ ልጄ እንደ ወልድ ትንሳኤህ እስኪገለጥ እርጋታን ገንዘብህ አድርግ!” ይለናል፡፡ በቃሉ ያባብለናል፡፡

የህማማት ቀናቶቻችን እንደ ግዮን ወንዝ የረዘሙ ሲመስሉ፣ የህዝባችን እፎይታ፣ የሀገራችን ሰላምና መረጋጋት እንደ ጌታችን መምጫ ቀን ሲርቁብን፣ ህይወት ከንቱ መኖርም ምናምንቴ መስሎ ሲታይ… የስጋ ድካም ከዘለዓለማዊው እጣ ፈንታችን ሊያናጥበን ሲል… ያን ጊዜ የታላላቅ አባቶች ምክር፣ የቅዱሳን ጥበብ፣ የታጋሾች ምስክርነት ያስፈልገናል፡፡

የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ አራት መጽሐፍት በአንድ ላይ
#እስከማዕዜኑ በሚል ርእስ የተዘጋጁትም ለዚሁ ዓላማ ነው፡፡

በሕይወታችን ያሉ እስከመቼ የምንልባቸውን መከራዎች እንዴት እንደምንወጣቸው የሚያስተምር ድንቅ መጽሐፍ ነው-
#እስከማዕዜኑ!

እስከማዕዜኑ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
የገፅ ብዛት - 304 የተለጠፈበት ዋጋ - 254 ብር
መሸጫ ዋጋ - 230 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263
+ + + ጽዋዔ በመምህር ያረጋል አበጋዝ ምልከታ + + +
ታላቁ አባት ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ አንጾኪያ በነበረበት ወቅት የአደረጋቸው ነገሮችና የአስተማራቸው ትምህርቶች ቤተ ክርስቲያን እና ሀገር በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ላይ በሚሆኑበት ጊዜ ሕዝብን እንዴት ማገልገልና አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ማሻገር እንደሚቻል በተግባር ያስተምሩናል፡፡
ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ሰፊ ጥናትና ዳሰሳ በማድረግ የአዘጋጀው ይኽ መጽሐፍ፤ በቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ የአንጾኪያ የተጋድሎ ሕይወት አንጻር ካህናት ሕዝባቸውን በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ እንዴት መምራትና ማሻገር እንደሚገባቸው ያሳየናል፡፡ ተግባራዊ ትምህርት የሚሰጥ የሆነውን ይህን መጽሐፍ በመጻፉም ሊመሰገን ይገባዋል፡፡
መምህር ያረጋል አበጋዝ
ጸሐፊና ሰባኬ ወንጌል


ጽዋዔ ዲያቆን ታደሰ ወርቁ
የገፅ ብዛት - 440 የተለጠፈበት ዋጋ - 385 ብር
መሸጫ ዋጋ - 340 ብር 🇪🇹 >= 3 Free delivery 🇪🇹
Contact us
@Guramayelie 0912319263