EECMY Children Ministry: MY Sunday School
725 subscribers
892 photos
14 videos
168 links
MY Sunday School is the official page of EECMY Children Ministry.

Wholistic Growth For Our Children!

Access Sunday School learning materials at www.mysundayschool.org
Download Telegram
ትውልድ በዕውቀት የምታነጽበት ቤተ መጻሕፍት ተመርቆ ተከፈተ...

EECMY- South West Bethel Synod:
Mizan Teferi Bethel Mekane Yesus

ቀጥለው ሙሉውን ያንብቡ

@MYSundaySchool
ቤተመጻሕፍት ተመርቆ ተከፈተ
#አንባቢዎች_መሪዎች_ናቸው
====
''የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል'' እንደሚለው ቃሉ (2ጢሞቴዎስ 3:16): በቤተክርስቲያኒቱ የልጆች እና ወጣቶች ሁለንተናዊ አገልግሎት ፓኬጅ መሰረት: ልጆች እና ወጣቶች: እንዲሁም አገልጋዮች እና መሪወች አንባቢዎች እንዲሆኑ: አንብበው እንዲማሩ: ተምረው እንዲያስተምሩ: ታድሰው ትውልዱን እንድያድሱ በማሰብ በእያንዳንዱ ማ/ምዕመናን መጠነኛ ቤተመጻሕፍት (Mini Library) እንዲደራጅ ታስቦ እና ታቅዶ እየተሰራበት ይገኛል።
ይኼንንም ራዕይ ተቀብለው ከግብ በማድረስ በደቡብ ምዕራብ ቤቴል ሲኖዶስ የምትገኘዋ የሚዛን ተፈሪ ቤቴል መካነ ኢየሱስ ማ/ምዕመናን ቀዳሚ ሆናለች።በሲኖዶሱ በነበረው የልጆች እና ወጣቶች የመሪዎች ስልጠና ወቅት የተደራጀውን ቤተመጻሕፍት ለእግዚአብሔር ክብር እና ለሰው ልጆች ጥቅም እንዲሆን በጸሎት መርቀን ከፍተናል።
ይሄንን ራዕይ ተቀብለው በቀዳሚነት ስላስፈጸሙት
የሚዛን ተፈሪ ቤቴል መካነ ኢየሱስ ማ/ምዕመናን የልጆች እና የወጣቶች አገልግሎት አስተባባሪዎችን: የማ/ምዐሰመናኗን ሽማግሌዎች: ቄሶች እና በወንጌላውያንን: መጽሐፍትን በመለገስ አስተዋጽኦ ያደረጉትን ሁሉ የሥራው ሁሉ ባለቤት እግዚአብሔር አምላክ አብዝቶ ይባርካችሁ ለማለት እንወዳለን።

ከዚህ በመቀጠል በከተማ ደረጃም ትውልዱን ወደ ዕውቀት ጎዳና የሚመራ ቤተመጻሕፍት ለማደራጀት የድርሻችሁን እንደምትወጡ ተስፋ እናደርጋለን። እኛ የዓለም ብርሃን እና የምድር ጨው እንድንሆን ተጠርተናልና ብርሃናችን ለሰው ሁሉ እንዲበራ ወደ ትውልዱ ወጥተን በመልካም ምግባራችን ብርሃን በመሆን እና ለምድሪቱም ጨው በመሆን ለእግዚአብሔር ክብር እና ለሰው ልጆች ጥቅም እንዲሆን መስራት አለብን።

👉የወጣቱ ትልቁ ሀብት አዕምሮው ነው: አዕምሮ ደግሞ የሚገነባው እና የሚበለጽገው በእውቀት ነው: ከእውቀት ምንጮች ዋነኛው ደግሞ መጽሐፍ ነው። አንባቢ ትውልድ መሪ ነው (Readers are Leaders) እንደሚባለው ልጆች እና ወጣቶች መሪ ሆነው እንዲያድጉ ሁላችንም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል።

👉ውድ ወጣቶች: መሪዎች: (አገልጋዮች)... በዚህ አጋጣሚ ሌሎች ማ/ምዕመናናትም ይሄን መልካም ተሞክሮ በመውሰድ: ትውልዱን ወደ ዕውቀት ጎዳና ለመምራት የሚፈይደውን በእያንዳንዱ ማ/ምዕመናን መጠነኛ ቤተመጻሕፍት (Mini Library)
ማደራጀት አለብን ብለን የጀመርነውን ራዕይ ከግብ እንድታደርሱ በጌታ ፍቅር አደራ ልንላችሁ እንወዳለን።በሚዛን ተፈሪ ቤቴል መካነ ኢየሱስ ያለውን እንቅስቃሴ አይተን ደስ ብሎናል። ትምህርቱ: ስልጠናው: ጉብኝቱ ይቀጥላል።

#ቤተ_መጽሐፍትን በማ/ም ደረጃ ለማደራጀት:
👉በየ ማ/ም ካሉት መጠነኛ ክፍል (ቢሮ) መጠቀም ይቻላል (የግድ አዲስ ግንባታ አያስፈልግም)
👉መጽሐፍትን የማሰባሰብ እንቅስቃሴን በመጀመር ሰዎች መጽሐፍትን እንዲለግሱ ማድረግ ይቻላል።
👉የገቢ ማሰባሰቢያ በማድረግ ተጨማሪ አዳዲስ መጽሐፎችንም በየጊዜው አቅዶ መግዛት ይቻላል።
👉መጽሐፎቹ ለመንፈሳዊም እንዲሁም ለጠቅላላ እውቀት የሚረዱ ሳይንሳዊ መጽሐፎች: ለሁለንተናዊ አገልግሎት የሚረዱ እንዲሆኑ መስራት:
👉ኮሚቴ በማዋቀር አገልግሎቱ ፈጣን: ምቹ እና ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን ማድረግ ይቻላል።

#ቤተመጽሐፍቱ ተደራጅቶ ሲራ ሲጀምር:.
👉ልጆች ያነባሉ...
👉ወጣቶች ያነባሉ...
👉አገልጋዮች ያነባሉ...
👉መሪዎች ያነባሉ...
👉ምዕመኑ ያነባል...
👉አንባቢ ትውልድ ይፈጠራል; በዕውቀት ህይወቱን; ቤቱን: ቤተሰቡን: አገልግሎቱን: ድርጅቱን: ሀገሩን ይመራል።

''መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤...'' (ሉቃስ 24:45); የምታነቡትን እንድታስተውሉ አእምሮአችሁ በኢየሱስ ስም የተከፈተ ይሁን!
===
ይህ መልዕክት ለሌሎችም እንዲደርስ #Share በማድረግ ይተባበሩን።

የተለያዩ ትምህርቶችን ለማግኘት የሚከተለውን አድራሻችንን ይጠቀሙ👇!

http://www.mysundayschool.org
https://t.me/MYSundaySchool
https://t.me/eecmyyouthministry
Forwarded from EECMY Youth Ministry
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
BIBLE FOR ALL HUMAN KIND!

''I do all this for the sake of the gospel, that I may share in its blessings.'' 1Cor. 9:23

Did YOU KNOW 👇?
 The work of Bible translation is tied to the very beginning of the EECMY when two freed slaves, Hika (Onesimos) Nesib and Aster Gano, finished translating the Bible into their own Oromo language, the largest language in Ethiopian in 1899.
 There are 88 unique languages in Ethiopia
 Only 11 languages have a complete or full Bible in Ethiopia
 Today EECMY is leading 21 Bible translation projects
 EECMY is collaborating with many local and international partners in reaching a linguistic Communities with their heart language
 The Bible Translation works are being done in different forms, Written, Oral , sign Language, Audio-Visual
 EECMY is also endeavoring in engaging the communities with scripture through Literacy, oral Bible storytelling, Trauma healing and etc.


#EECMY_Lutheran_Bible_Translation
#EECMY_Department_of_Mission_and_Theology
👇👇👇
@eecmyyouthministry
Forwarded from EECMY Youth Ministry
''በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ።'' 1ቆሮ. 9:23
#መጽሐፍ_ቅዱስ_ለሰው_ልጆች_ሁሉ!

በአፍ መፍቻ ቋንቋ መጽሐፍ ቅዱስ አልዎት?
 በአፍ መፍቻ ቋንቋህ መጽሐፍ ቅዱስ ከሌሎዎት ሥራው እንዲጀመር በፀሎትና በገንዘብ ይርዱ!
 በአፍ መፍቻ ቋንቋዎች መጽሐፍ ቅዱስ ካሎት እርሶም የቀደምት አባቶች እና እናቶች ትጋት እና ፈለግ በመከተል እድሉ ያልደረሳቸውን እንዲደርሳቸው በፀሎት እና በገንዘብ ይርዱ!
 ይህንኑ ዓላማ ለማራመድ በየአመቱ በሰኔ ውር የመካነ ኢየሱስ ብሔራዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ሳምት ተብሎ እንዲከበር በቤተ ክርስቲያን ታውጇል፡፡ ስለዚህ በፊታችን ባለው ሰኔ 13 እስከ 19/2014 በሚከተለው ሁኔታ ይከበራል፡-
 መጽሐፍ ቅዱስን ለሌሎች በመስጠት
 የወንጌል አርበኞችን በማሰብና ሥራቸውን በመዘከር
 የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም ሥራ ላልተጀመረባቸው ቋንቋዎች ለመድረስ አስፈላጊውን የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ

''በወንጌል አላፍርምና፤ ... ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና።'' ሮሜ 1:16

#EECMY_Lutheran_Bible_Translation
#EECMY_Department_of_Mission_and_Theology


@eecmyyouthministry
Forwarded from EECMY Youth Ministry
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
Kana Beektuu Laata!

• Jalqabbiin Waldaa Makaana Yesuus, Hiika Awaajii (Oneesimoos Nasiib) fi Asteer Gannoon garbummaa jalaa bilisa ba’aniin booda Afaan dhaloota isaanii kan ta’e Afaan Oromoon bara 1899 Macaafa Qulqulluu hiikanii xumuruu isaanii waliin wal-qabata.
• Biyya ltiyoophiyaa keessa afaan garaa garaa 88’tu argama.
• Garuu Macaafa Qulqulluu guutummaatti hiikame kan qabaatan Afaan 11 qofaa dha.
• Ammaan kana waldaan Makaana Yesuus Hojii Hiikkaa Macaafa Qulqulluu afaan 21’n hojjechuurratti argamti.
• Saba daneessa biyya kana keessa jiran afaan dhalootaa isaaniitiin Dubbii Waaqayyoo biraan ga’uufis dhaabbilee gara garaa biyya keessaa fi biyya alaa waliin taatee hojjechaa jirti.
• Hojiin Hiikaa Macaafa Qulqulluu tooftaa garaaqaraatiin kan adeemisfamu yoo ta’u isaanis, barreefama, sagalee, afaan mallattoo argaa-dhageettiidhaan.
• Akkasumas WWWMYesuus Sagalee Waaqayyo hawaasa bal’aa biraan ga’uudhaaf karaa barnoota ga’eessotaa, seenaa Macaafa Qulqulluu dubbiidhan himuu fi kkf ifaajii guddaa taasisaa jirti.
ውድ ወንድማችን ፀጋሁን አሰፋ

የኢት/ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ ዋና ጽ/ቤት የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት ዳይሬክተር በመሆን ከ2013-2021 እ.ኤ.አ በትጋት እና በታማኝነት እግዚአብሔርን እና ህዝቡን ስላገለገልክ የሥራው ባለቤት ጌታ እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርክህ! ቤተሰብህ አገልግሎትህ እና ቀሪው የሕይወት ዘመንህ ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም የተባረከ ይሁን፡፡ አሜን!

‹‹ እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስካሁንም ስለምታገለግሉአቸው ያደረጋችሁትን ሥራ ስለ ስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና ::›› ዕብ.6፡10

የኢት/ወ/ቤ/ክ/መ/ ኢየሱስ የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት ዲፓርትመንት

ግንቦት 2022 አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ

🙏🙏🙏

Jaalatamaa Obboleessa keenya Tsaggaahuun Asaffaa

WWW Makaana Yesuus Waajjira Olaanaatti Daarikteera Tajaajila Ijoollee fi Dargaggoo ta'uudhaan bara 2013-2021 ALA amanamummaa fi ciminaan Waaqayyoo fi saba Isaa waan tajaajilteef abbaan hojichaa Waaqayyo Gooftaan guddisee sihaa eebbisuu! Maatiinkee, tajaajillikee fi barri jireenyakee kan eebbifame haa ta'u!

''Waaqayyo hojii keessanii fi isa jaallachuu keessan... argisiiftan hin irraanfatu, hin jal'isus.'' Ibr. 6:10

WWW Makaana Yesuus Itoophiyaa- Tajaajila Ijoollee fi Dargaggoo

Caamsaa 2022, Finfinnee, Itoophiyaa


@MYSundaySchool
Forwarded from Wondmagegn Udessa Bidire
ከኢት/ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ ፕረዚዳንቶች ጋር...

';የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው።''  ዕብራውያን 13:7

እግዚአብሔር ቤተሰቦቻችሁን: አገልግሎታችሁን እና ዘመናችሁን አብዝቶ ይባርክ🙏!
===👇👇👇👇
''Warra isin geggeessanii, dubbii Waaqayyoo isinitti himanii turan yaadadhaa! Attamitti akka jiraatan akka du'anis, jireenya isaanii keessaa wanta argames ilaalaa, fakkeenya amantii isaanii fudhadhaa duukaa bu'aa!'' Ibroota 13:7

Pirezidaantota WWW Makaana Yesuus Itoophiyaa waliin...

Waaqayyo Gooftaan maatii, tajaajilaa fi bara keessan hundumaan dachaan haa eebbisuu, Nuuf Jiraadhaa🙏!
===👇👇👇👇
''Remember your leaders, who spoke the word of God to you. Consider the outcome of their way of life and imitate their faith.'' Hebrews 13:7
With EECMY Presidents since 1991
1. Rev. Yadesa Daba 1991-2001
2. Rev. Itefa Gobena 2001-2009
3. Rev. Dr. Wakseyoum Idossa 2009-2017
4. Rev.Dr. Yonas Yigezu, Since 2017

May God bless you, your family and your ministry abundantly! #Long_Live🙏!