EECMY Children Ministry: MY Sunday School
757 subscribers
904 photos
14 videos
171 links
MY Sunday School is the official page of EECMY Children Ministry.

Wholistic Growth For Our Children!

Access Sunday School learning materials at www.mysundayschool.org
Download Telegram
EECMY National Bible Week Celebration! June 19-26, 2022

የመጽሐፍ ቅዱስ ሳምንት: ሰኔ 12-19,2014 ዓ.ም

Torbaan Kitaaba Qulqulluu, Waxabajjii 12-19, 2014ALI
ለልጆች እና ወጣቶች ቤተ መጻሕፍት 200 መጽሐፍቶችን ያበረከቱ አባት...አቶ አቤል ዶርቴት
===
ቤተመጻሕፍትን (Mini Library)
በእያንዳንዱ ማ/ም የማደራጀት ራዕይ እና እንቅስቃሴ ...

👇👇👇 ቀጥለው ያንብቡ👇

===
MANA KITAABAA IJOOLLEE FI DARGAGGOOTIIF KITAABOTA 200 GUMAACHAN...Obbo Abeel Dorteet...

===
👉Mul'ataa fi sochii Manneen Kitaabaa (Mini Library) waldoota Kiristaanaa (manneen sagadaa) hundumaa keessatti jalqabsiisuu...

👇👇👇Itti fufaatii dubbifadhaa...eebbifamaa!


👇👇👇
t.me/MYSundaySchool
ለልጆች እና ወጣቶች ቤተ መጻሕፍት 200 መጽሐፍቶችን ያበረከቱ አባት...አቶ አቤል ዶርቴት
===
አቶ አቤል ዶርቴት ይባላሉ። በአዲሱ ደቡብ ምዕራብ ክልል: ቤንች ሸኮ ዞን: ሚዛን ተፈሪ ከተማ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ይኖራሉ። ከመምህርነት ጀምረው በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ለአራት አስርት አመታት ህዝብን እና መንግስትን አገልግለዋል። በሚያመልኩበት እና በሚያገለግሉበት የመካነ አየሱስ ቤተ ክርስቲያንም በተለያየ የሃላፊነት ስፍራ አገልግለዋል: አሁንም እያገለገሉ ይገኛሉ።
በየ እያንዳንዱ ማህበረ ምዕመናን ቤተ መጻሕፍትን ማደራጀት እና ማስጀመር በሚል ራዕይ የጀመርነውን እንቅስቃሴ በመደገፍ በሚዛን ተፈሪ ቤቴል መካነ ኢየሱስ ማ/ም ለዚሁ አገልግሎት ድጋፍ እንዲውል ለሁለንተናዊ እድገት የሚረዱ 200 መጽሐፍቶችን አበርክተዋል። ጋሽ አቤል: ለዚህ መልካም ተግባርዎ ትውልድ ያመሰግንዎታል። በነዚህ መጽሐፍት ታንጸው እና አድገው ለቁም ነገር የበቁትን እንዲያዩ በሙሉ ጤንነት እና ረጅም እድሜ እግዚአብሔር ይባርኮት! ኑሩልን!

ልጆች እና ወጣቶቻችን በሁለንተናዊ እድገት ታንጸው እንዲያድጉ የልጆች እና የወጣቶች አገልግሎት ድፓርትመንት ሁለንተናዊ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ፓኬጅ አዘጋጅቶ እየሰራበት ይገኛል። ከፓኬጁ አንዱ አካዳሚክ ኤክሰለንሲ (Academic Excellency) ነው; ማለትም ልጆች እና ወጣቶች በእውቀት እና በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው እንዲያድጉ መስራት ነው።

የወጣቱ ትልቁ ሀብት አዕምሮው ነው: አዕምሮ ደግሞ የሚገነባው እና የሚበለጽገው በእውቀት ነው: ከእውቀት ምንጮች ዋነኛው ደግሞ መጽሐፍ ነው። አንባቢ ትውልድ መሪ ነው (Readers are Leaders) እንደሚባለው ልጆች እና ወጣቶች መሪ ሆነው እንዲያድጉ ሁላችንም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል።

👉ውድ ወጣቶች: መሪዎች: (አገልጋዮች)...
በእያንዳንዱ ማ/ም ከትንሽ ጀምሮ (Mini Library) ቤተ መጽሐፍትን እንድታደራጁ እና ትውልዱን ወደ እውቀት ጎዳና በመምራት የድርሻችሁን እንድትወጡ አደራ እንላችኋለን። በሚዛን ተፈሪ መካነ ኢየሱስ ያለውን እንቅስቃሴ አይተን ደስ ብሎናል። ትምህርቱ: ስልጠናው: ጉብኝቱ ይቀጥላል።

#ቤተ_መጽሐፍትን በማ/ም ደረጃ ለማደራጀት:
👉በየ ማ/ም ካሉት መጠነኛ ክፍል (ቢሮ) መጠቀም ይቻላል (የግድ አዲስ ግንባታ አያስፈልግም)
👉መጽሐፍትን የማሰባሰብ እንቅስቃሴን በመጀመር ሰዎች መጽሐፍትን እንዲለግሱ ማድረግ ይቻላል።
👉የገቢ ማሰባሰቢያ በማድረግ ተጨማሪ አዳዲስ መጽሐፎችንም በየጊዜው አቅዶ መግዛት ይቻላል።
👉መጽሐፎቹ ለመንፈሳዊም እንዲሁም ለጠቅላላ እውቀት የሚረዱ ሳይንሳዊ መጽሐፎች: ለሁለንተናዊ አገልግሎት የሚረዱ እንዲሆኑ መስራት:
👉ኮሚቴ በማዋቀር አገልግሎቱ ፈጣን: ምቹ እና ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን ማድረግ ይቻላል።

#ቤተመጽሐፍቱ ተደራጅቶ ሲራ ሲጀምር:.
👉ልጆች ያነባሉ...
👉ወጣቶች ያነባሉ...
👉አገልጋዮች ያነባሉ...
👉መሪዎች ያነባሉ...
👉ምዕመኑ ያነባል...
👉አንባቢ ትውልድ ይፈጠራል; በዕውቀት ህይወቱን; ቤቱን:  ቤተሰቡን: አገልግሎቱን: ድርጅቱን: ሀገሩን ይመራል።

''መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤...'' (ሉቃስ 24:45); የምታነቡትን እንድታስተውሉ አእምሮአችሁ በኢየሱስ ስም የተከፈተ ይሁን!
===
ይህ መልዕክት ለሌሎችም እንዲደርስ #Share/Forward በማድረግ ይተባበሩን።

የተለያዩ ትምህርቶችን ለማግኘት የሚከተለውን አድራሻችንን ይጠቀሙ👇!

http://www.mysundayschool.org
https://t.me/MYSundaySchool
https://t.me/eecmyyouthministry
MANA KITAABAA IJOOLLEE FI DARGAGGOOTIIF KITAABOTA 200 GUMAACHAN...
===
Obbo Abeel Dorteet jedhamu. Naannoo haaraa dhiyeenyatti hundeeffame, M.Naannoo Kibba Lixa Itoophiyaa, Godina Beenchi Shakkootti, Magaalaa Miizaan Tafarii keessa maatii isaanii waliin jiraatu. Barsiisummaarraa jalqabuudhaan waggoottaan kurnan afran darbaniif ogummaa garagaraatiin uummataa fi mootummaa tajaajilaniiru.  Waldaa Kiristaanaa keessatti tajaajilanii fi keessatti WWWMakaana Yesuus Beeteel Miizaaniittis itti gaafatamummaa garagaraatiin tajaajilaniiru, tajaajiluu irrattis argamu.
Mul'ata Manneen kitaabaa waldoota hundumaatti jalqabsiisuu jennee akka tajaajila ijoollee fi dargaggootti sochii  jalqabneen: mul'ata kana deeggaruudhaaf Waldaa Makaana Yesuus Beeteel Miizaan Tafariitti argamtutti Kitaabilee guddina hundagaleessaaf gargaaran 200 gumaachaniiru. Maanguddoo keenya: hojii gaarii hojjattan kanaaf dhalootni isin galateeffata. Dhaloota kitaabilee kanneeniin sammuun isaa ijaaramee, jireenyisaa haaromfamee bakka gaarii gaarii gahe akka argitaniif Waaqayyo Gooftaan umrii dheeraa fi fayyaa guutuudhaan isin nuuf eebbisuu! Nuuf jiraadhaa!

Ijoollee fi dargaggoon keenya guddina hundagaleessaan ijaaramanii akka guddataniif jecha kutaan tajaajila ijoollee fi dargaggoo Paakeejii Hundagaleessa Ijoollee fi Dargaggoo qopheessee irratti hojjachaa jira. Paakeejii keessaa inni tokko hojii sammuu dhalootaa misoomsuuti (Academic Excellency). Kaayoon isaas ijoollee fi dargaggoon keenya beekumsaa fi amala/naamusa gaariidhaan ijaaramanii akka hojjataniif deeggaruudha. 

Qabeenyi guddaan dargaggootaa sammuu isaaniiti. Sammuun immoo kan ijaaramuufi kan misoomu beekumsaani. Maddoota beekumsaa keessaa inni guddaan immoo kitaabadha. Dhalootni dubbisu dhaloota gaggeessuudha (Readers are Leaders) akkuma jedhamu, ijoollee fi dargaggootni keenya gaggeessitoota ta'anii akka nuuf guddataniif gahee keenya haa baanu.

👉Jaalatamoo dargaggoota, gaggeessitoota (tajaajiltoota)...waldoota/ manneen sagadaa hundumaa keessatti manneen kitaabaa (mini library) hundeessuudhaan dhaloota gara daandii beekumsaa fi milkaa'inaatti gaggeessuu keessatti gahee keessan akka baataniif jaalalaan waamicha isiniif dhiyeessina. Waldaa Makaana Yesuus Beeteel Miizaan Tafariitti jalqabbii gaarii arginee gammadnee jirra. Barsiisni, leenjiinii fi daawwannaan itti fufa...!

#Mana_Kitaabaa  hundeessuudhaaf:
👉Kutaa (gola waajjiraa), isuma waldaa keessatti ijaarramee jiru keessaa tokkotti fayyadamuudhaan waanuma xiqqaarraa jalqabuun nidanda'ama (jalqabuudhaaf dirqama mana haaraa ijaaruun hin barbaachisu, isuma jirutti fayyadamuun jalqabuun nidanda'ama.)
👉Sochii gumaata kitaabotaa jalqabsiisuudhaan namootni kitaabota akka gumaachaniif sochii taasisuun nidanda'ama.
👉Sagantaa galii walitta qabuu garagaraa qopheessuudhaan tajaajila kanaaf deeggarsa sassaabuudhaan kitaabola haaraa yeroo yeroodhaan karooraan bitanii dabaluun nidanda'ama.
👉Kitaabbilee hafuuraa fi saayinsaawaa ta'an, beekumsa walii galaatii fi guddina hundagaleessa dhalootaatiif kan ta'an akka ta'an irratti hojjachuun gaarii ta'a!
👉Koree hundeessuudhaan tajaajilli mana kitaabichaa mijataa fi hawwataa akka ta'u gochuun nidanda'ama.

#Manni_Kitaabichaa tajaajila kennuu yoo jalqabu;
👉Ijoolleen nidubbisu,
👉Dargaggootni nidubbisu,
👉Gaggeessitootni nidubbisu,
👉Tajaajiltootni nidubbisu,
👉Amantootni nidubbisu,
👉Walumaa galatti dhalootni dubbisu ni uumama, dhalootni dubbisu immoo beekumsaan jireenyasaa, manasaa, maatiisaa, tajaajilasaa, dhaabbatasaa, biyyasaa gaggeessa.
''...kitaabota haa hubataniif sammuu isaanii baneef...'' (Luq. 24:45) jedhamee akkuma barreeffametti, kitaanota dubbistan hubattanii beekumsaa fi ogummaadhaan akka guddattaniif Waaqayyo sammuu keessan haa banu!
===
Ergaan kun dhaloota bira akka gahuuf #Share/Forward gochuun tajaajila kana deeggaraa!

👉Barumsa garagaraa kallattiin argachuuf, miidiyaa keenya hawaasaa kanneen fayyadama.


http://www.mysundayschool.org
https://t.me/MYSundaySchool
https://t.me/eecmyyouthministry
በኢት/ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ የአዶላ ገናሌ ሲኖዶስ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ክፍል አስተባባሪ የነበሩት ቄስ ጌሎ ጎሎሎልቻ የሲኖዶሱ ፕረዚዳንት ሆነው እንዲያገለግሉ በመመረጥዎ መልካም የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንልዎ እንመኛለን! የሥራው ባለቤት እግዚአብሔር ጥበብን እና ማስተዋሉን ያብዛልዎት! አሜን!

የዋና ጽ/ቤት የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ክፍል

WWWMakaana Yesuus Itoophiyaa, Sinoodoosii Adoolaa Gannaaleetti Qindeessaa Kutaa Tajaajila Ijoollee fi Dargaggoo kan turan Lubni Geeloo Gololchaa Pireezidaantii Sinoodoosichaa ta'uudhaan filamuu keessaniif bara tajaajila gaarii isiniif hawwina. Abbaan hojii Waaqayyo Gooftaan kallattii hundumaan isin haa gargaaruu! Mul'ataa fi ogummaas isiniif haa baay'isuu! Ameen.

Tajaajila Ijoollee fi Dargaggoo WWWMYI
እግዚአብሔር ዓለምን ፈጠረ (ዘፍጥረት 1)
🌎🌒🌞🌛🐦🦚🦜🦆🦄🦋🐅🐏🐄🌴🌾🍃🍇🍓🍃🌻🍉👫👨‍👩‍👧‍👦

ቀጥላችሁ አንብቡ!👇
እግዚአብሔር ዓለምን ፈጠረ (ዘፍጥረት 1)
🌎🌒🌞🌛🐦🦚🦜🦆🦄🦋🐅🐏🐄🌴🌾🍃🍇🍓🍃🌻🍉👫👨‍👩‍👧‍👦
ውድ ልጆች በያላችሁበት የእግዚአብሔር ሰላም ይብዛላችሁ! ከብዙ ዘመናት በፊት ይህ ዓለም አልነበረም፡፡ ወፎች፣ ንቦች ሜዳና አበቦችም አልነበሩም፡፡ ሐይቆች ወንዞች ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትም  አልበሩም ሰዎችም አልነበሩም ሰዎችም አልነበሩም ምንም ነገር አልነበረም፡፡ እግዚአብሔር ብቻ ነበር፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ምድርን ፈጠረ፡፡ ሰማይና ምድርን ፈጠረ ሁሉን ነገር ከማይታይ ነገር ፈጠረ እግዚአብሔር ዓለምን በውስጧ ያለውን ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ ፈጠራቸው አንዳንዱን በአንድ ቀን ፈጠረ እግዚአብሔር ማኛውንም ነገር ሲፈጥር ‹‹ እንዲህ ይሁን››ይል ነበር፡፡ ያም ነገር ይሆናል፡፡

በመጀመሪያ ጨለማ በሁሉም ስፍራ ነበር ስለሆነም እግዚአብሔር ‹‹ ብርሃን ይሁን አለ›› እግዚአብሔር ይህንን እንዳለ ሆነ፡፡ ብርሃኑም የቀን ብርሃን ነበር ይህም የመጀመሪው ቀን ነው፡፡ በሚቀጥለው ቀን እግዚአብሔር ሰማዩን ከእኛ በላይ ከፍ እንዲል ተናገረው እርሱም ሆነ  ይህም ሁለተኛ ቀን ነበር፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ውሃ በአንድ ስፍራ እንዲሰበሰብ አዘዘ በዚህም መንገድ ወንዞችን ባሕሮችን እና ውቅያኖስን ፈጠረ፡፡ በመካከላቸውም ደረቅ ምድረ በዳ ሆነ፡፡

ነገር ግን በምድር ላይ አንዳች ነገር አልበቀለም ነበር፡፡ ዛፎችና ቁጥቋጦዎች ወይም አበቦች በየትኛውም ሥፍራ አልነበሩም፡፡ እግዚአብሔር ተናገረ እፅዋትን ፈጠረ፡፡ ሜዳዎች ሁሉ አረንጓዴ ሣር ለበሱ፡፡ የሚያማምሩና ብዙ ዓይነት ቀለም ያላቸው አበባዎች በመሬት ላይ በቀሉ ቁጥቋጦዎችና ዛፎች በየዓይነቱ ነበሩ፡፡ ብዙዎቹ ቁጥቋጦዎችና ዛፎችም ፍሬዎች ነበሩአቸው፡፡እግዚአብሔር ለእፅዋቶቹ ዘርን ሰጣቸው ስለሆነም ሁልጊዜ ብዙ እፅዋት ያድጋሉ፡፡እግዚአብሔር እነዚህን ሁሉ በሦስተኛው ቀን አደረገ፡፡

እግዚአብሔር ከዚህ የበለጠ ፈጥሮአል እግዚአብሔር ተናገረ ሰማይም በአንድ ግዜ በብርሃን ተሞላ ፀሐይና ጨረቃን በሌሊትም የሚያብለጨልጩትን ከዋክብት ፈጠረ፡፡ ይህም በአራተኛው ቀን ሆነ፡፡ ምድር አሁን የምታምር ሆነች እግዚአብሔር ከዚህም የተሸለች አድርጓታል እግዚአብሔር አንድ ጊዜ ደግሞ ተናገረና ዓሣንና በባሕር ውስጥ የሚኖሩትን ልዩ ልዩ ወፎች ሞላቸው እግዚአብሔር እነዚህን ሁሉ በአምስተኛው ቀን አደረገ፡፡

በስድስተኛው ቀን እግዚአብሔር እንደገና ተናገረ፡፡ ንቦች ከአንዱ አበባ ወደ ሌላው እንዲበሩ አደረገ፡፡ ድመቶችና ውሾች በሜዳ ላይ ይጫወታሉ ፈረሶችና ላሞች ምግባቸውን እየፈለጉ ወዲያና ወዲህ ይሉ ነበር፡፡

እግዚአብሔር ሁሉንም ዓይነት እንሰሶች በምድር ላይ የሚመላለሱ ፍጥረታትን ሁሉ እንዲሁም የምድር አራዊትን ሁሉ ፈጠረ፡፡ በመጨረሻም እግዚአብሔር ሰዎችን ፈጠረ፡፡ እግዚአብሔር የመጀመሪያውን ሰውን ከምድር አፈር አበጀው እንዲሁም በአፍንጫው እፍ አለበት፡፡ እግዚአብሔር ቀጥሎ የመጀመሪያውን ሴት ለመጀመሪያው ሰው እረዳት እንድትሆን ፈጠራ፡፡ እግዚአብሔር የመጀመሪያዋን ሴት የፈጠራት ከአዳም የጎድን አጥንቶች አንዱን በመውሰድ ነው፡፡ እግዚአብሔር ከፈጠራት በኋላ ሚስት እንድትሆነው ወደ አዳም አመጣት አዳምም ሔዋን ብሎ ስም አወጣላት፡፡ እግዚአብሔር የፈጠራቸውን ሁሉ ተመለከተ እንሆ ሁሉም መልካም ነበር በሰባተኛው ቀን እግዚአብሔር ከሥራው ሁሉ አረፈ ሰባተናውንም ቀን ባረከው ቀደሰውም፡፡

1. እግዚአብሔር ዓለምን በስንት ቀናት ውስጥ ፈጠረ?
2. በየቀኑ የፈጠራቸውን ጥራ?
3. እግዚአብሔር የፈጠራቸው የመጀመሪያው ወንድና የመጀመሪያው ሴት እነማን ነበሩ?

መልሳችሁን በሃሳብ መስጫ ቦታው ላይ ጻፉ!

መልካም እና የተባረከ ቀን ይሁንላችሁ!

http://www.mysundayschool.org
https://t.me/MYSundaySchool