AddisWalta - AW
45.5K subscribers
42.1K photos
208 videos
20 files
16.7K links
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
Download Telegram
የታለመለት የነዳጅ ድጎማ ተግባራዊ መሆን ጀመረ

ሰኔ 29/2014 (ዋልታ) የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሸከርካሪዎችን ብቻ ተጠቃሚ የሚያደርገው የታለመለት የነዳጅ ድጎማ ከዛሬ ሰኔ 29 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ከ160 ሺሕ በላይ ተሽከርካሪዎች ላይ ተግባራዊ መሆን መጀመሩን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።

በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተሸከርካሪዎች የታለመለት የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ ለመሆን አስፈላጊ መረጃዎችን በመስጠት በኢትዮ ቴሌኮም የሽያጭ ማዕከላት በኩል ምዝገባ ማድረጋቸውን ሚኒስቴሩ አስታውሷል።

የብሔራዊ የታለመለከት የነዳጅ ድጎማን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ በኢትዮ ቴሌኮም በኩል መተግበሪያ በልፅጎ አስተማማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ነው ሚኒስቴሩ ያስታወቀው።

በዚህም መሠረት በቴሌ ብር በኩል አገልግሎቱን ለማግኘት የተመዘገቡ ከ160 ሺሕ በላይ ተሸከርካሪዎች ከዛሬ ጀምሮ መተግበሪያውን በመጠቀም ይስተናገዳሉ ተብሏል።

የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎች ዓመታዊ የነዳጅ ፍጆታ ተቀራራቢ የሊትር መጠን ግምት በጥናት መለየቱና እያንዳንዱ ተሸከርካሪ የሚጠቀመውን የነዳጅ መጠን ያገናዘበ ስሌት በመቀመጡ ተሽከርካሪዎቹ ያለብክነት የታለመ የነዳጅ ድጎማን ጥቅም ላይ እንዲያውሉ የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።

በዚህም መሰረት
- ባለሦስት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) በቀን 7 ሊትር
- መለስተኛ የከተማ ታክሲ (ላዳ) በቀን 25 ሊትር
- ሚኒባስ ታክሲ በቀን 65 ሊትር
- መለስተኛ አውቶብስ በቀን 94 ሊትር
- የከተማ አውቶብስ በቀን 102 ሊትር
- የሕዝብ አውቶብስ በቀን 25 ሊትር
- ሀገር አቋራጭ አውቶብስ በቀን 65 ሊትር ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ሚኒስቴሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።
እንደምን አደርሽ ኢትዮጵያ ከዋልታ ቴቪ ሰኔ 29/2014
https://fb.watch/e4TJ-lf1Zr/
በክልሉ ግንባታቸው ባልተጠናቀቁ ማደያዎች በህገወጥ መንገድ የተከማቸ ነዳጅ ተያዘ

ሰኔ 29/2014 (ዋልታ) በአማራ ክልል እንጅባራ ከተማ አስተዳደርና ሰሜን ሜጫ ወረዳ ግንባታቸው ባልተጠናቀቁ ማደያዎች በህገ-ወጥ መንገድ የተከማቸ ነዳጅ መያዙን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በቢሮው የንግድ ውድድርና ሸማቾች ጥበቃ መሠረታዊ ዕቃዎች ጉዳይ ዳይሬክተር ታፈረ ይመር ለኢዜአ እንደገለጹት ነዳጁ ሊያዝ የቻለው ከቢሮው፣ ከዞን፣ ከወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች በተዋቀረ ቡድን በተደረገ ክትትል ነው።

በእንጅባራ ከተማ አስተዳደር በተደረገ ክትትል ግንባታው ባልተጠናቀቀ ማደያ 184 ሺሕ ሊትር ነዳጅ መገኘቱን ገልጸው ከነዳጁ ውስጥ 46 ሺሕ ሊትር የሚሆነው ቤንዚን ሲሆን ቀሪው ናፍጣ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተመሳሳይ በምዕራብ ጎጃም ዞን ሰሜን ሜጫ ወረዳ ልዩ ቦታው ጉንጫ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ በአራት ቦቴ የተገለበጠ ነዳጅ በህገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ መገኘቱን አመልክተዋል።

በሁለቱም ቦታዎች ተደብቆ የተገኘው ነዳጅ በአንድ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት የቀረበና ግንባታቸው ባልተጠናቀቁ ሁለት ማደያዎች እንደተገኘ አብራርተዋል።

“ማደያዎቹ ከክልል ጀምሮ ከዞን፣ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር ከተሰጣቸው የግንባታ ፈቃድ ውጭ ገና ህጋዊ ዕውቅና ያላገኙና የማጠራቀሚያ ታንከር ብቻ የተቀበረባቸው መስፈርቱን ያላሟሉ ናቸው” ብለዋል።

ነዳጁ የስርጭት አግባቡን ያልተከተለ፣ ባልተጠናቀቀ ማደያ ያለዕውቅና የተከማቸና ለአደጋ በሚያጋልጥ መልኩ የተቀመጠ መሆኑን አስረድተዋል።
https://www.facebook.com/489211707826282/posts/pfbid0iwQt61dJr4DsCU4KY4kF5m9UkBnsWgETbTMft47Zz8DA9bbSRbSk5p5eVh2BX9iGl/?app=fbl
በከተማዋ ከ190 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተሰሩ ፕሮጀክቶች እየተመረቁ ነው

ሰኔ 29/2014 (ዋልታ) በኦሮሚያ ክልል ባቱ ከተማ ከ190 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተሰሩ ፕሮጀክቶች እየተመረቁ ነው።

በኦሮሚያ ክልል ገንዘብ ቢሮ ኃላፊ ቶሎሳ ገደፋ የተመራ ልዑክ በባቱ ከተማ በበጀት ዓመቱ ሲሰሩ የነበሩትን የተለያዩ ፕሮጀክቶች እያስመረቀ ይገኛል።

በባቱ ከተማ አስተዳደር በበጀት ዓመቱ ከ190 ሚሊየን በላይ ወጪ ከተሰሩ ፕሮጀክቶች መካከል 70 ፕሮጀክቶች ተጠናቀው በዛሬው እለት እየተመረቁ እንደሚገኙ ነው የተገለጸው።

ተሰርተው በመጠናቀቅ እየተመረቁ ካሉ ፕሮጀክቶች መካከልም 35 ሚሊየን በሚጠጋ ወጪ የተሰሩ የ2ኛ ደረጃ ኢፈ ቦሩና ቡዑረ ቦሩ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ 13 ነጥብ 8 ኪ.ሜ የኮብል ሰቶን መንገድ፣ 3 ነጥብ 6 ኪ.ሜ የሚረዝምና 5 ሚሊየን ብር በሚጠጋ ወጪ የተሰሩ የመንገድ መብራት ማስፋፍያም ዋነኞቹ ናቸው።

በባቱ ከተማ እየተካሄደ ባለው የፕሮጀክት ምርቃት ላይ ከክልል የተወጣጡ ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮችን ጨምሮ የባቱ ከተማ ማኅበረሰብም እየተሳተፉበት ይገኛል።

ታምራት ደለሊ (ከባቱ)

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
31 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ

ሰኔ 29/2014 (ዋልታ) ኮይካ ባደረገው የገንዘብ ድጋፍ በዩኒሴፍ የተገዙ 31 ሚሊየን ብር የሚያወጡ የእናቶችና የጨቅላ ህፃናት ሞት ለመቀነስ እና ጤናቸው ለማሻሻል የሚያግዙ የህክምና መርጃ ቁሳቁስ ለጤና ሚኒስቴር ድጋፍ ተድርጓል።

መድሃኒት ፣ አልጋና ሞተርሳይክልን ጨምሮ 33 ዓይነት የህክምና ቁሳቁሶች ናቸው ድጋፍ የተደርጉት።

የህክምና ቁሳቁሶቹ ለአፋርና ቤንሻንጉል ክልሎች ይሰራጫሉም ተብሏል።

ድጋፉን የተቀበሉት የጤና ሚንስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ድጋፉ የእናቶችና ህፃናት ሞትን ለመቀነስ እና ጤናቸውን ለማሸሻል ያግዘናል ብለዋል።

በትእግስት ዘላለም
ፓርላማው ዛሬ ባካሄደው 6ኛው ልዩ ስብሰባ በወቅታዊ የፀጥታ እና በንጹሐን ዜጎች ጉዳይ ላይ ተወያይቶ የውሳኔ ሐሳብ አሳለፈ

ሰኔ 29/2014 (ዋልታ) የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ኛው ልዩ ስብሰባ ፤ በወቅታዊ የፀጥታ እና በንጹሐን ዜጎች ጉዳይ ላይ ተወያይቶ የውሳኔ ሐሳብ አስተላለፈ።

የዕለቱን መርኃ-ግብር በግፍ ለተጨፈጨፉት ዜጎች የአንድ ደቂቃ የኅሊና ጸሎት በማድረግ የጀመረው ምክር ቤት፤ የሚከተሉትን የውሳኔ ሐሳቦች አስተላልፏል፡፡

በዜጎች ላይ የተፈጸመውን ጭፍጨፋ እጅግ የኮነነው ምክር ቤቱ በሀገሪቱ በየትኛውም ክልልና አካባቢ በሲቪል ዜጎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት ያስከተሉ እና ንብረት ያወደሙ ግለሰቦች በሕግ እንዲጠየቁ እንዲደረግ ሲል ውሳኔ አሳልፏል።

በየደረጃው ያለው አመራር አካል፣ የጸጥታ አካል እና የፍትሕ ተቋም የሕዝቡን ደኅንነትና ሠላም በጥብቅ እንዲያስከብር፣ አጥፊዎች ለሕግ ተጠያቂነት እንዲቀርቡ እንዲደረግ ወስኗል።

ከመንደራቸውና ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ የማቋቋም ሥራ በአስቸኳይ እንዲሰራ የወሰነው ምክር ቤቱ፤ የኢትዮጵያ ሕዝቦች በዚህ በአስቸጋሪ ወቅት ከየትኛውም ጊዜ በላይ በወንድማማችነት፣ በአብሮነት እና በአንድነት እንዲቆሙ መልዕክቱን አስተላልፏል።
ርዕሰ መስተዳድሩ ለሕዝብ ተጠቃሚነት በላቀ ቁርጠኝነት መንቀሳቀስ ያስፈልጋል አሉ

ሰኔ 29/2014 (ዋልታ) ለሕዝብ ተጠቃሚነት በላቀ ቁርጠኝነት መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ አስታወቁ፡፡

የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት (ካቢኔ) በ2014 ዓ.ም የሴክተር መስሪያ ቤቶች አፈፃፀም እና የ2015 በጀት ዓመት አማራጭ የበጀት ድልድል ላይ ተወያይቷል።

ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ የክልሉ መንግሥት ለሕዝብ የገባውን ቃል ከመፈፀም አንፃር የተለያዩ ተግባራት ቢከናወኑም በቀጣይ በላቀ ትኩረት መንቀሳቀስ ይገባል ብለዋል።

በክልሉ የኑሮ ውድነትን ከማረጋጋት አንፃር እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን ማጠናከርና ቀጣይነት ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

ከቅጥርና ከደረጃ እድገት ጋር በተያያዘም የህግ ጥሰት በሚፈፅሙ እና በኢንቨስትመንት ስም መሬት ወስደው ባላለሙ አካላት ላይም በአፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
https://www.facebook.com/489211707826282/posts/pfbid0tzA5JDFcnituPrpSpcnsBS4KY7Uq4uwLJfHa5UVurEmtVA4VNFxEFtrLjs6ibSVZl/
ከሐምሌ 1 - 10 ቀን ከፍተኛ ጎርፍ ሊከሰት ስለሚችል በተዳፋት አካባቢዎች ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ኢንስቲትዩቱ አሳሰበ

ሰኔ 29/2014 (ዋልታ) በሐምሌ ወር የመጀመሪያዎቹ አስር ቀናት ከፍተኛ ጎርፍ ስለሚኖር በተዳፋትና ገደላማ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አሳሰበ፡፡

ኢንስቲትዩቱ ከሐምሌ 1 እስከ 10 ቀን 2014 ዓ.ም የሚኖረውን የአየር ፀባይ ሁኔታ ትንበያ በተመለከተ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

በመግለጫውም በሐምሌ ወር የመጀመሪያዎች አስር ቀናት በሀገሪቱ መደበኛ እና በአንዳንድ አካባቢዎች ነጎድጓዳማ እና በረዶ የቀላቀለ ዝናብ ይጠበቃል ብሏል።

በትንበያው መሰረት በሚቀጥሉት አስር ቀናት የሚኖረው የዝናብ ሁኔታ ከባድ እና ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል መሆኑን ገልጿል።

በዚህም በምዕራባዊ የሀገሪቱ አካባቢዎች አጋማሽ እና መካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከ100 እስከ 200 ሚሊ ሜትር፤ በተወሰኑ ቦታዎች ከ200 ሚሊ ሜትር በላይ ዝናብ እንደሚጠበቅ በመግለጫው ተመላክቷል፡፡

በሐምሌ ወር በመጀመሪያዎቹ አስር ቀናት በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በትግራይ እና በደቡብ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች መደበኛ እና ከመደበኛ በላይ ዝናብ ይጠበቃል ብሏል።

በአብዛኛው የአባይ፣ ባሮ-አኮቦ፣ ተከዜ፣ አዋሽ፣ ስምጥ ሸለቆ፣ ኦሞጊቤ፣ አፋር-ዳናከል፣ የላይኛውና መካከለኛው ዋቢ-ሸበሌ እንዲሁም ገናሌ-ዳዋ ተፋሰሶች ከፍተኛ እርጥበት ይኖራቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።

በታችኛው ገናሌ-ዳዋ፣ ስምጥ ሸለቆ እና ...
https://www.facebook.com/489211707826282/posts/pfbid02ztXiMb61dneWUTfdou1RVecH6ZjQktBdq2HyqJGNPz4UaU4YCB1MBN42RrQTy6NAl/
ከስደት ተመላሽ ዜጎች የተሻለ ኑሮን ለመፍጠር ከዓለም ዐቀፉ የፍልሰት ድርጅት የላቀ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ

ሰኔ 29/2014 (ዋልታ) ከፍልሰት ጋር የተገናኙ ተግዳሮቶች በዘላቂነት ለመፍታት እና ለተመላሽ ዜጎች የተሻለ ኑሮን ለመፍጠር ከዓለም ዐቀፉ የፍልሰት ድርጅት የላቀ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ከዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት የምስራቅ አፍሪካና እና አፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ዳይሬክተር መሀመድ አብዲከር ጋር በፍልሰት እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ሊኖር ስለሚገባ የጋራ ትብብር ውይይት አድርገዋል፡፡

በውይይታቸው አምባሳደር ብርቱካን ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት እና በትብብር በመስራት ለሀገሪቱ የፍልሰት አስተዳደርና በተመላሸ ዜጎች ዙሪያ የሚደረገውን ጥረት እያደረገ ያለውን ያልተቋረጠ ድጋፍ አድንቀዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በውጭ አገር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ወደ አገራቸው ለመመለስና ህገ-ወጥ ስደትን ለመቀነስ ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል።
https://www.facebook.com/489211707826282/posts/pfbid0Y6nykWorhwST1pFMAmBVzWytA2vmY7oafkaKZZDCyyrPmFbL6f2ZqfnmngBAsoml/
የስምንተኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እየወሰዱ ያሉ የ65 አመቷ አዛውንት

ሰኔ 29/2014 (ዋልታ) የ2014 ዓ.ም የስምንተኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና መስጠት ከትናንት በስቲያ መጀመሩ ይታወቃል።

በደቡብ ክልልም ፈተናው ከትናንት ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል።

በክልሉ ደቡብ ኦሞ ዞን በጂንካ ኔሪ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በማታው ክፍለ ጊዜ ትምህርታቸውን በመከታተል የሚገኙት የ65 ዓመቷ ወርቅነሽ ወንበራ የስምነተኛ ክፍል ፈተናን በመውሰድ ላይ መሆናቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
የስራ እና ክህሎት ሚኒስትሯ ከዓለም ዐቀፉ የስደተኞች ድርጅት የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

ሰኔ 29/2014(ዋልታ) የስራ እና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል ከዓለም ዐቀፉ የስደተኞች ድርጅት የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ሙሀመድ አብዲከር ጋር ተወያዩ፡፡

ሚኒስትሯ ከጊዜ ወደ ጊዜ አሳሳቢነቱ እየጨመረ በመጣው ቀጣናዊና ሀጉራዊ በሆኑ የሠራተኞች ፍልሰት ጉዳዮች ላይ ፣ በቀጠናው የክህሎት ልማት እና የወጣቶች የሥራ ዕድለ ፈጠራን፣ የሰራተኞች ተዘዋውሮ የመስራት፣ የዜጎችን ሰብዓዊ እና ማህበራዊ መብቶችን ማስጠበቅን በተመለከተ መወያየታቸውን አስታውቀዋል፡፡

ኢትዮጵያ በቀጠናው የሰራተኞች ፍልሰት ጉዳይ የሚኒስትሮች ፎረምን የምትመራ ሀገር እንደመሆኗ ድርጅቱ ድጋፉን አጠናክሮ ስለሚቀጥልበት ሁኔታም መምከራቸውን ከትስስር ገጻቸው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ከቀጠናው ባለፈ ከሌሎች ሀገራት እና አህጉራት ጋር ህጋዊ የሆነ የሰለጠነና በከፊል የሰለጠነ የሰው ኃይል ዝውውር ሥርዓት መዘርጋት እና በትብብር ለመስራት በሚደረገው እንቅስቃሴ ድርጅቱ ድጋፉን እንደሚጠናክር ማረጋገጡን ጠቁመዋል፡፡
የዓለም ምግብ ፕሮግራም በአፋር ክልል ከ650 ሺሕ በላይ ለሆኑ ወገኖች የምግብ እርዳታ እያደረገ መሆኑን ገለጸ

ሰኔ 29/2014(ዋልታ) የዓለም ምግብ ፕሮግራም በአፋር ክልል ከ650 ሺሕ በላይ ለሆኑ ወገኖች የምግብ እርዳታ እያቀረበ መሆኑን አስታወቀ።

የድርጅቱን አስቸኳይ የምግብ እርዳታ የጫኑ ተሽከርካሪዎች በሰሜናዊ አፋር ኮኔባ አካባቢ ዛሬ መድረሳቸውን እና ወደ መጋዘን እየተራገፈ እንደሚገኝ በማህበራዊ ትስስር ገጹ አመላክቷል።

በየስድስት ሳምንት ልዩነት “በአፋር ክልል በግጭትና በድርቅ ምክንያት” ለተፈናቀሉ ከ650 ሺሕ በላይ ወገኖች ድጋፍ እያደረገ እንደሆነም ጠቁሟል።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ባለፈው ሳምንት በክልሉ ለ80 ሺሕ ዜጎች የሚሆን የምግብ እርዳታ ማድረሱን ጠቁሞ አሁንም የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚቀጥል ገልጿል።