EECMY Children Ministry: MY Sunday School
748 subscribers
894 photos
14 videos
169 links
MY Sunday School is the official page of EECMY Children Ministry.

Wholistic Growth For Our Children!

Access Sunday School learning materials at www.mysundayschool.org
Download Telegram
ለልጆች እና ወጣቶች ቤተ መጻሕፍት 200 መጽሐፍቶችን ያበረከቱ አባት...አቶ አቤል ዶርቴት
===
አቶ አቤል ዶርቴት ይባላሉ። በአዲሱ ደቡብ ምዕራብ ክልል: ቤንች ሸኮ ዞን: ሚዛን ተፈሪ ከተማ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ይኖራሉ። ከመምህርነት ጀምረው በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ለአራት አስርት አመታት ህዝብን እና መንግስትን አገልግለዋል። በሚያመልኩበት እና በሚያገለግሉበት የመካነ አየሱስ ቤተ ክርስቲያንም በተለያየ የሃላፊነት ስፍራ አገልግለዋል: አሁንም እያገለገሉ ይገኛሉ።
በየ እያንዳንዱ ማህበረ ምዕመናን ቤተ መጻሕፍትን ማደራጀት እና ማስጀመር በሚል ራዕይ የጀመርነውን እንቅስቃሴ በመደገፍ በሚዛን ተፈሪ ቤቴል መካነ ኢየሱስ ማ/ም ለዚሁ አገልግሎት ድጋፍ እንዲውል ለሁለንተናዊ እድገት የሚረዱ 200 መጽሐፍቶችን አበርክተዋል። ጋሽ አቤል: ለዚህ መልካም ተግባርዎ ትውልድ ያመሰግንዎታል። በነዚህ መጽሐፍት ታንጸው እና አድገው ለቁም ነገር የበቁትን እንዲያዩ በሙሉ ጤንነት እና ረጅም እድሜ እግዚአብሔር ይባርኮት! ኑሩልን!

ልጆች እና ወጣቶቻችን በሁለንተናዊ እድገት ታንጸው እንዲያድጉ የልጆች እና የወጣቶች አገልግሎት ድፓርትመንት ሁለንተናዊ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ፓኬጅ አዘጋጅቶ እየሰራበት ይገኛል። ከፓኬጁ አንዱ አካዳሚክ ኤክሰለንሲ (Academic Excellency) ነው; ማለትም ልጆች እና ወጣቶች በእውቀት እና በመልካም ስነ ምግባር ታንጸው እንዲያድጉ መስራት ነው።

የወጣቱ ትልቁ ሀብት አዕምሮው ነው: አዕምሮ ደግሞ የሚገነባው እና የሚበለጽገው በእውቀት ነው: ከእውቀት ምንጮች ዋነኛው ደግሞ መጽሐፍ ነው። አንባቢ ትውልድ መሪ ነው (Readers are Leaders) እንደሚባለው ልጆች እና ወጣቶች መሪ ሆነው እንዲያድጉ ሁላችንም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል።

👉ውድ ወጣቶች: መሪዎች: (አገልጋዮች)...
በእያንዳንዱ ማ/ም ከትንሽ ጀምሮ (Mini Library) ቤተ መጽሐፍትን እንድታደራጁ እና ትውልዱን ወደ እውቀት ጎዳና በመምራት የድርሻችሁን እንድትወጡ አደራ እንላችኋለን። በሚዛን ተፈሪ መካነ ኢየሱስ ያለውን እንቅስቃሴ አይተን ደስ ብሎናል። ትምህርቱ: ስልጠናው: ጉብኝቱ ይቀጥላል።

#ቤተ_መጽሐፍትን በማ/ም ደረጃ ለማደራጀት:
👉በየ ማ/ም ካሉት መጠነኛ ክፍል (ቢሮ) መጠቀም ይቻላል (የግድ አዲስ ግንባታ አያስፈልግም)
👉መጽሐፍትን የማሰባሰብ እንቅስቃሴን በመጀመር ሰዎች መጽሐፍትን እንዲለግሱ ማድረግ ይቻላል።
👉የገቢ ማሰባሰቢያ በማድረግ ተጨማሪ አዳዲስ መጽሐፎችንም በየጊዜው አቅዶ መግዛት ይቻላል።
👉መጽሐፎቹ ለመንፈሳዊም እንዲሁም ለጠቅላላ እውቀት የሚረዱ ሳይንሳዊ መጽሐፎች: ለሁለንተናዊ አገልግሎት የሚረዱ እንዲሆኑ መስራት:
👉ኮሚቴ በማዋቀር አገልግሎቱ ፈጣን: ምቹ እና ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን ማድረግ ይቻላል።

#ቤተመጽሐፍቱ ተደራጅቶ ሲራ ሲጀምር:.
👉ልጆች ያነባሉ...
👉ወጣቶች ያነባሉ...
👉አገልጋዮች ያነባሉ...
👉መሪዎች ያነባሉ...
👉ምዕመኑ ያነባል...
👉አንባቢ ትውልድ ይፈጠራል; በዕውቀት ህይወቱን; ቤቱን:  ቤተሰቡን: አገልግሎቱን: ድርጅቱን: ሀገሩን ይመራል።

''መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤...'' (ሉቃስ 24:45); የምታነቡትን እንድታስተውሉ አእምሮአችሁ በኢየሱስ ስም የተከፈተ ይሁን!
===
ይህ መልዕክት ለሌሎችም እንዲደርስ #Share/Forward በማድረግ ይተባበሩን።

የተለያዩ ትምህርቶችን ለማግኘት የሚከተለውን አድራሻችንን ይጠቀሙ👇!

http://www.mysundayschool.org
https://t.me/MYSundaySchool
https://t.me/eecmyyouthministry
MANA KITAABAA IJOOLLEE FI DARGAGGOOTIIF KITAABOTA 200 GUMAACHAN...
===
Obbo Abeel Dorteet jedhamu. Naannoo haaraa dhiyeenyatti hundeeffame, M.Naannoo Kibba Lixa Itoophiyaa, Godina Beenchi Shakkootti, Magaalaa Miizaan Tafarii keessa maatii isaanii waliin jiraatu. Barsiisummaarraa jalqabuudhaan waggoottaan kurnan afran darbaniif ogummaa garagaraatiin uummataa fi mootummaa tajaajilaniiru.  Waldaa Kiristaanaa keessatti tajaajilanii fi keessatti WWWMakaana Yesuus Beeteel Miizaaniittis itti gaafatamummaa garagaraatiin tajaajilaniiru, tajaajiluu irrattis argamu.
Mul'ata Manneen kitaabaa waldoota hundumaatti jalqabsiisuu jennee akka tajaajila ijoollee fi dargaggootti sochii  jalqabneen: mul'ata kana deeggaruudhaaf Waldaa Makaana Yesuus Beeteel Miizaan Tafariitti argamtutti Kitaabilee guddina hundagaleessaaf gargaaran 200 gumaachaniiru. Maanguddoo keenya: hojii gaarii hojjattan kanaaf dhalootni isin galateeffata. Dhaloota kitaabilee kanneeniin sammuun isaa ijaaramee, jireenyisaa haaromfamee bakka gaarii gaarii gahe akka argitaniif Waaqayyo Gooftaan umrii dheeraa fi fayyaa guutuudhaan isin nuuf eebbisuu! Nuuf jiraadhaa!

Ijoollee fi dargaggoon keenya guddina hundagaleessaan ijaaramanii akka guddataniif jecha kutaan tajaajila ijoollee fi dargaggoo Paakeejii Hundagaleessa Ijoollee fi Dargaggoo qopheessee irratti hojjachaa jira. Paakeejii keessaa inni tokko hojii sammuu dhalootaa misoomsuuti (Academic Excellency). Kaayoon isaas ijoollee fi dargaggoon keenya beekumsaa fi amala/naamusa gaariidhaan ijaaramanii akka hojjataniif deeggaruudha. 

Qabeenyi guddaan dargaggootaa sammuu isaaniiti. Sammuun immoo kan ijaaramuufi kan misoomu beekumsaani. Maddoota beekumsaa keessaa inni guddaan immoo kitaabadha. Dhalootni dubbisu dhaloota gaggeessuudha (Readers are Leaders) akkuma jedhamu, ijoollee fi dargaggootni keenya gaggeessitoota ta'anii akka nuuf guddataniif gahee keenya haa baanu.

👉Jaalatamoo dargaggoota, gaggeessitoota (tajaajiltoota)...waldoota/ manneen sagadaa hundumaa keessatti manneen kitaabaa (mini library) hundeessuudhaan dhaloota gara daandii beekumsaa fi milkaa'inaatti gaggeessuu keessatti gahee keessan akka baataniif jaalalaan waamicha isiniif dhiyeessina. Waldaa Makaana Yesuus Beeteel Miizaan Tafariitti jalqabbii gaarii arginee gammadnee jirra. Barsiisni, leenjiinii fi daawwannaan itti fufa...!

#Mana_Kitaabaa  hundeessuudhaaf:
👉Kutaa (gola waajjiraa), isuma waldaa keessatti ijaarramee jiru keessaa tokkotti fayyadamuudhaan waanuma xiqqaarraa jalqabuun nidanda'ama (jalqabuudhaaf dirqama mana haaraa ijaaruun hin barbaachisu, isuma jirutti fayyadamuun jalqabuun nidanda'ama.)
👉Sochii gumaata kitaabotaa jalqabsiisuudhaan namootni kitaabota akka gumaachaniif sochii taasisuun nidanda'ama.
👉Sagantaa galii walitta qabuu garagaraa qopheessuudhaan tajaajila kanaaf deeggarsa sassaabuudhaan kitaabola haaraa yeroo yeroodhaan karooraan bitanii dabaluun nidanda'ama.
👉Kitaabbilee hafuuraa fi saayinsaawaa ta'an, beekumsa walii galaatii fi guddina hundagaleessa dhalootaatiif kan ta'an akka ta'an irratti hojjachuun gaarii ta'a!
👉Koree hundeessuudhaan tajaajilli mana kitaabichaa mijataa fi hawwataa akka ta'u gochuun nidanda'ama.

#Manni_Kitaabichaa tajaajila kennuu yoo jalqabu;
👉Ijoolleen nidubbisu,
👉Dargaggootni nidubbisu,
👉Gaggeessitootni nidubbisu,
👉Tajaajiltootni nidubbisu,
👉Amantootni nidubbisu,
👉Walumaa galatti dhalootni dubbisu ni uumama, dhalootni dubbisu immoo beekumsaan jireenyasaa, manasaa, maatiisaa, tajaajilasaa, dhaabbatasaa, biyyasaa gaggeessa.
''...kitaabota haa hubataniif sammuu isaanii baneef...'' (Luq. 24:45) jedhamee akkuma barreeffametti, kitaanota dubbistan hubattanii beekumsaa fi ogummaadhaan akka guddattaniif Waaqayyo sammuu keessan haa banu!
===
Ergaan kun dhaloota bira akka gahuuf #Share/Forward gochuun tajaajila kana deeggaraa!

👉Barumsa garagaraa kallattiin argachuuf, miidiyaa keenya hawaasaa kanneen fayyadama.


http://www.mysundayschool.org
https://t.me/MYSundaySchool
https://t.me/eecmyyouthministry
ቤተመጻሕፍት ተመርቆ ተከፈተ
#አንባቢዎች_መሪዎች_ናቸው
====
''የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል'' እንደሚለው ቃሉ (2ጢሞቴዎስ 3:16): በቤተክርስቲያኒቱ የልጆች እና ወጣቶች ሁለንተናዊ አገልግሎት ፓኬጅ መሰረት: ልጆች እና ወጣቶች: እንዲሁም አገልጋዮች እና መሪወች አንባቢዎች እንዲሆኑ: አንብበው እንዲማሩ: ተምረው እንዲያስተምሩ: ታድሰው ትውልዱን እንድያድሱ በማሰብ በእያንዳንዱ ማ/ምዕመናን መጠነኛ ቤተመጻሕፍት (Mini Library) እንዲደራጅ ታስቦ እና ታቅዶ እየተሰራበት ይገኛል።
ይኼንንም ራዕይ ተቀብለው ከግብ በማድረስ በደቡብ ምዕራብ ቤቴል ሲኖዶስ የምትገኘዋ የሚዛን ተፈሪ ቤቴል መካነ ኢየሱስ ማ/ምዕመናን ቀዳሚ ሆናለች።በሲኖዶሱ በነበረው የልጆች እና ወጣቶች የመሪዎች ስልጠና ወቅት የተደራጀውን ቤተመጻሕፍት ለእግዚአብሔር ክብር እና ለሰው ልጆች ጥቅም እንዲሆን በጸሎት መርቀን ከፍተናል።
ይሄንን ራዕይ ተቀብለው በቀዳሚነት ስላስፈጸሙት
የሚዛን ተፈሪ ቤቴል መካነ ኢየሱስ ማ/ምዕመናን የልጆች እና የወጣቶች አገልግሎት አስተባባሪዎችን: የማ/ምዐሰመናኗን ሽማግሌዎች: ቄሶች እና በወንጌላውያንን: መጽሐፍትን በመለገስ አስተዋጽኦ ያደረጉትን ሁሉ የሥራው ሁሉ ባለቤት እግዚአብሔር አምላክ አብዝቶ ይባርካችሁ ለማለት እንወዳለን።

ከዚህ በመቀጠል በከተማ ደረጃም ትውልዱን ወደ ዕውቀት ጎዳና የሚመራ ቤተመጻሕፍት ለማደራጀት የድርሻችሁን እንደምትወጡ ተስፋ እናደርጋለን። እኛ የዓለም ብርሃን እና የምድር ጨው እንድንሆን ተጠርተናልና ብርሃናችን ለሰው ሁሉ እንዲበራ ወደ ትውልዱ ወጥተን በመልካም ምግባራችን ብርሃን በመሆን እና ለምድሪቱም ጨው በመሆን ለእግዚአብሔር ክብር እና ለሰው ልጆች ጥቅም እንዲሆን መስራት አለብን።

👉የወጣቱ ትልቁ ሀብት አዕምሮው ነው: አዕምሮ ደግሞ የሚገነባው እና የሚበለጽገው በእውቀት ነው: ከእውቀት ምንጮች ዋነኛው ደግሞ መጽሐፍ ነው። አንባቢ ትውልድ መሪ ነው (Readers are Leaders) እንደሚባለው ልጆች እና ወጣቶች መሪ ሆነው እንዲያድጉ ሁላችንም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል።

👉ውድ ወጣቶች: መሪዎች: (አገልጋዮች)... በዚህ አጋጣሚ ሌሎች ማ/ምዕመናናትም ይሄን መልካም ተሞክሮ በመውሰድ: ትውልዱን ወደ ዕውቀት ጎዳና ለመምራት የሚፈይደውን በእያንዳንዱ ማ/ምዕመናን መጠነኛ ቤተመጻሕፍት (Mini Library)
ማደራጀት አለብን ብለን የጀመርነውን ራዕይ ከግብ እንድታደርሱ በጌታ ፍቅር አደራ ልንላችሁ እንወዳለን።በሚዛን ተፈሪ ቤቴል መካነ ኢየሱስ ያለውን እንቅስቃሴ አይተን ደስ ብሎናል። ትምህርቱ: ስልጠናው: ጉብኝቱ ይቀጥላል።

#ቤተ_መጽሐፍትን በማ/ም ደረጃ ለማደራጀት:
👉በየ ማ/ም ካሉት መጠነኛ ክፍል (ቢሮ) መጠቀም ይቻላል (የግድ አዲስ ግንባታ አያስፈልግም)
👉መጽሐፍትን የማሰባሰብ እንቅስቃሴን በመጀመር ሰዎች መጽሐፍትን እንዲለግሱ ማድረግ ይቻላል።
👉የገቢ ማሰባሰቢያ በማድረግ ተጨማሪ አዳዲስ መጽሐፎችንም በየጊዜው አቅዶ መግዛት ይቻላል።
👉መጽሐፎቹ ለመንፈሳዊም እንዲሁም ለጠቅላላ እውቀት የሚረዱ ሳይንሳዊ መጽሐፎች: ለሁለንተናዊ አገልግሎት የሚረዱ እንዲሆኑ መስራት:
👉ኮሚቴ በማዋቀር አገልግሎቱ ፈጣን: ምቹ እና ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን ማድረግ ይቻላል።

#ቤተመጽሐፍቱ ተደራጅቶ ሲራ ሲጀምር:.
👉ልጆች ያነባሉ...
👉ወጣቶች ያነባሉ...
👉አገልጋዮች ያነባሉ...
👉መሪዎች ያነባሉ...
👉ምዕመኑ ያነባል...
👉አንባቢ ትውልድ ይፈጠራል; በዕውቀት ህይወቱን; ቤቱን: ቤተሰቡን: አገልግሎቱን: ድርጅቱን: ሀገሩን ይመራል።

''መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤...'' (ሉቃስ 24:45); የምታነቡትን እንድታስተውሉ አእምሮአችሁ በኢየሱስ ስም የተከፈተ ይሁን!
===
ይህ መልዕክት ለሌሎችም እንዲደርስ #Share በማድረግ ይተባበሩን።

የተለያዩ ትምህርቶችን ለማግኘት የሚከተለውን አድራሻችንን ይጠቀሙ👇!

http://www.mysundayschool.org
https://t.me/MYSundaySchool
https://t.me/eecmyyouthministry
EECMY Children Ministry: MY Sunday School
ኢየሱስ  እና ማዕበሉ (ሉቃስ 8፣ማቴዎስ 8፣ ማርቆስ 4) YESUUSII FI BUBBEE JABAA (Luqaas 8, Maatewos 8, Maarqos 4) 👇 👇 👇 https://t.me/MYSundaySchool
ኢየሱስ  እና ማዕበሉ
(ሉቃስ 8፣ማቴዎስ 8፣ ማርቆስ 4)
===
ኢየሱስ ሲያስተምር ለመስማት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደ እርሱ ይመጡ ነበር፡፡ አንዳንዶች እርዳታውን ለመጠየቅ ይመጡ ነበር፡፡ አንዳንዶች ደግሞ ወደ መንግሥተ ሰማያት መግባት እንዴት እንደሚቻል ለመመር ይፈልጉ ነበር አንዳንድ የታመሙ ደግመሞ ጤናማ መሆን ይፈልጉ ነበር አንዳንድ ግዜ ኢየሱስ ምግብ ለመብላት እንኳጊዜ እስኪያጣ ድረስ ያጨናንቁት ነበር፡፡

ከአድካሚ ቀን በኋላ ኢየሱስ በገሊላ ባህር አጠገብ ነበር፡ ለማረፍ ፈለገ:: ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ‹‹ ከሕዝቡ ተለይተን ጥቂት ጊዜ ማረፍ አለብን›› አላቸው፡፡ ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ በታንኳ ተሳፍሪው ሐይቁን ማቋረጥ ጀመሩ ኢየሱስ በጀልባው የኋላ ክፍል ተኝቶ ነበር፡፡

ወዲያው ማዕበሉ ሐይቁን አናወጠው ሰማዩ ጠቆረ : ነፋሱም በኃይል መንፈስ ጀመረ ሞገዱ እየጨመረ መጣ: ጀልባው በውሃ ይሞላ ጀመር፡፡ ደቀመዛሙርቱ ፈሩ ያለጥርጥር ታንኳው ይሰምጣል ብለው አሰቡ፡፡

ኢየሱስን ቀሰቀሱትና ‹‹ጌታ ሆይ አድነን›› አሉት፡፡ ኢየሱስም በፍቅር ተመለከታቸው ‹‹ እኔ ሁልግዜ እንደምረዳችሁ አታውቁምን? ታዲያ ለምን ፈራችሁ? ብሎ ጠየቃቸው፡፡ ከዚያም ኢየሱስ ንፋሱንና ባሕሩን ‹‹ሰላም ይሁን ጸጥ በል›› ብሎ አዘዘው፡፡  ወዲያው ንፋሱም አቆመ፣ ባሕሩም ጸጥ አለ፡፡ ደቀ መዛመርቱ ‹‹ንፋሱንና ባሕሩ የሚታዘዝለት ኢየሱስ ማነው? ብለው ጠየቁ፡፡

ውድ ልጆች፡ ኢየሱስ ማዕበልና ንፋስም ሁሉ የሚታዘዙለት እውነተኛ እና ዘላለማዊ ጌታችን ነው፡፡ በህይወታችሁ ማንኛውም ዓይነት ማዕበል ሲያጋጥማችሁ አትፍሩ፡ ለጌታ ኢየሱስ ንገሩት፡ የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉ፡ እርሱ በነገር ሁሉ ይረዳችኋል፡፡
===
ውድ ልጆች: በሚቀጥሉት ጥያቄዎች ላይ ከወላጆቻችሁ ጋር ውይይት አድርጉ። መልካም እና የተባረከ ሳምንት ይሁንላችሁ!

ኢየሱስ ፍጹም ሰው መሆኑን የሚያሳይ ምን አደረገ?
ኢየሱስ አምላክ መሆኑን ለማሳየት ምን አደረገ?

This is the Official Channel of EECMY Children Ministry
#Follow #Forward #Share
https://t.me/MYSundaySchool
EECMY Children Ministry: MY Sunday School
ኢየሱስ  እና ማዕበሉ (ሉቃስ 8፣ማቴዎስ 8፣ ማርቆስ 4) YESUUSII FI BUBBEE JABAA (Luqaas 8, Maatewos 8, Maarqos 4) 👇 👇 👇 https://t.me/MYSundaySchool
YESUUSII FI BUBBEE JABAA
(Luqaas 8, Maatewos 8, Maarqos 4)

Namootni kumaatamni barsiisa Isaa dhaga’uuf gara Yesuus ni dhufan. Kaanimmoo gargaarsa Isa gaafachuuf dhufan. Namootni garri tokko attamitti mootummaa Waaqayyootti galuun akka danda’amu baruu barbaadan. Garri kaan immoo dhukkubsatoo waan turaniif fayyina barbaadu. Si’a tokko tokko namootni kun Yesuus hanga yeroo nyaataa dhabutti Isa muddaa turan.

Guyyaa dhiphaa sana booddee, Yesuus naannoo Galaana Galiilaa ture. Waan dadhabeef boqochuu ni barbaade. Yesuus duuka buutota Isaatiin akkas jedhe, “Kottaa me haroo kana gara gamatti ceenaa. Namoota kana irraa adda baanee yeroo xiqqoo boqochuu qabna.”

Yesuusii fi duuka-buutotni isaa bidiruu tokko yaabbatanii haroo sana ce’uu ni jalqaban. Yesuusis bidiricha gara duubaatiin ni rafe.

Yeroodhuma sana dhahaan galaanaa haroo sana irra bubbisuu jalqabe. Samiin ni gurraacha’e. Qilleensi ciminaan bubbise. Dhahaan bishaanii ol ka’aa adeeme. Bishaan bidirichatti guutuu jalqabe.
Duuka buutotni ni sodaatan. Isaan bidirichi dhugumatti ni liqimsama jedhanii yaadan.
Isaan Yesuusiin dammaqsanii akkas jedhan,”Gooftaa nu’oolchi!”

Yesuus gara-laafinaan gara firoota isaa ilaalee akkas jedhee isaan gaafate,”Maaliif sodaattani? Ani yeroo hundumaa iyyuu akkan isin gargaaru hin beektanii?”

Itti aansee Yesuus qilleensichaa fi dhaha galaanichatti dubbate. Akkasis jedhe, “Cal jedhi, Gab jedhi.”

Battalumatti qillensichi bubbisuu ni dhaabe, galaanicha irrattis gabiitu ta’e.

Duuka-buutotni Isaas akkas jedhanii gaafatan, “Yesuus kun eenyu? Qilleensii fi galaanni illee kan abboomamuuf.”

Yaa ijoollee, Yesuus Inni Gooftaa barabaraa qilleensii fi bubbeen kamuu abboomamuufiidha/ajajamuufiidha. Jireenya keessan keessatti qilleensii fi bubbeen kamuu yoo isin mudate hin sodaatinaa, hin dhiphatinaa. Gooftaa Yesuusitti himadhaa, Isatti dabarsaatii laadhaa. Inni waan isin dhiphisu kamuu isinirraa kaasa, rakkina keessan hundumaatti isin gargaara.
Ijoollee gaaffilee asii gadii kanneen irratti warra keessan waliin irratti mari’adhaa. Torbaan Gaarii isiniif haa ta’u!

1.  Yesuus eenyummaa isaa qabatamaa ta’e akka qabu wanta agarsiisu maal hojjete?
2.  Yesuus Waaqayyo akka ta’e agarsiisuudhaaf maal hojjate?

This is the Official Channel of EECMY Children Ministry
#Follow #Forward #Share
https://t.me/MYSundaySchool
ኢትዮጵያ በቅርቡ ከአውሮፓ ህብረት ጋራ የፈረመችውን ስምምነት በመቃወም የተዘጋጀ የፊርማ ማሰባሰቢያ ቅጽ
        * ⚠️ አስቸኳይ⚠️  *
ባሳለፍነው ህዳር 5 ቀን 2016 ዓም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ከካሪቢያንና ከፓሲፊክ የተውጣጡ ሀገራት ለሚቀጥሉት 20 ዓመታት የሚቆይ የንግድና ኢኮኖሚ ትብብር ስምምነትን ከአውሮፓ ህብረት ጋራ ሳሞዋ በምትባል ሀገር በፈረሙ ወቅት አገራችን ኢትዮጵያም ይህንኑ ስምምነት ተቀማጭነታቸው ብራሰልስ በሆኑ አምባሳደV አማካኝነት በፊርማዋ አጽድቃለች፡፡ ይህ አደገኛ ይዘቶች ያሏቸውን አንቀጾች የያዘው ስምምነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ ከሚቀጥለው ጥር ወር ጀምሮ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡

ይህ የትብብር ስምምነት በውሥጡ የያዛቸውን አስራ ሁለት ዋና ዋና አደገኛ ይዘቶችን ጠቅልለው የሚይዙ የተወሰኑ ሀሳቦች ለመጥቀስ ያህል ፡-

ሀ) የሀገር ሉዓላዊነትን የሚጥሱ አንቀጾች በግልጽ መቀመጣቸው፣

ለ) ግብረሰዶማዊነት፣ የጾታ መቀየርና፣¸ውርጃና ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርትን የመሳሰሉ እኩይ አጀንዳዎች በሰብዓዊ መብት ሽፋንና በሌሎች አሳሳች ሀረጎች ተሰውረው የገቡበት መሆኑ፣

ሐ) ግብረሰዶማዊነት በርካታ ቀውሶች ማለትም በአካል፣ በሥነልቦናና በማህበራዊ ህይወት ላይ የሚያስከትልና ለሀገር ደህንነትም አደጋ መሆኑ፣

መ) የወላጆችን መብት የሚጥስና የኢትዮጵያዊ ቤተሰብ እሴቶችን የሚንድ መሆኑ፣

ሠ) የሀገራችንን ሀይማኖት፣ባህልና እሴቶች የሚንዱ ጸያፍ ልምምዶችን እንድንቀበል በሰብዓዊ መብት ሽፋንና በእርዳታ ስም የምንገደድበትና ለዘመናዊ ባርነት ወይንም ቅኝ አገዛዝ ታልፈን የምንሰጥበት መሆኑ፣

በአጠቃላይ ይህ አዲስ የአጋርነት ስምምነት ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡና ትውልድንና ብሎም ሀገርን እጅግ የሚጎዱ በርካታ አንቀጾች የተካተቱበት መሆኑ ለሀገራችን ህዝብ ዕድገትን ሳይሆን ውድቀትንና ከፍተኛ የሞራል ዝቅጠትን የሚያስከትል መሆኑን በሚገባ ተረድተናል፡፡

በተጨማሪም ከተጠበቀው ውጭ ሀገራችን ይህንን ስምምነት በመፈረJ የተጋረጠብንን እጅግ አሳሳቢ አደጋ ለመቀልበስ አስፈላጊ የሆኑ ሰላማዊና ህጋዊ መንገዶችን ሁሉ በመጠቀም መንግስት ትኩረትን እንዲሰጠው ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡

በመሆኑም ይህ የመንግስት ውሳኔ እንደገና ተጠንቶ ውሳኔው እንዲቀለበስ ማለትም ስምምነቱ አስፈላጊው ሁሉ ማስተካከያ እስኪደረግበት ድረስ ወይንም እጅግ አደገኛ የሆኑት አንቀጾች ተነቅሰው ወጥተው የማንቀበላቸው መሆናችንን በይፋ ማሳወቅ (Submission of an Interpretive Declaration) እስከምንችል ድረስ የምንወዳት ሐገራችን ኢትዮጵያ ፊርማዋን በመሰረዝ ከስምምነቱ ራሷን እንድታገልል በሐገራችን ከፍተኛው የሥልጣን አካል ለሆነው ለተከበረው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለሐገሪቱ መሪ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በታላቅ አክብሮት እጅግ አስቸኳይ ጥሪን እናደርጋለን፡፡

የዚህንም ስምምነት አደገኛ አንቀጾችንና በኤክስፐርቶች የተሰጠውን ትንታኔ የያዘ ዶኩመንት በአባሪነት ያቀረብን መሆናችንንም በታላቅ አክብሮት እንገልጻለን፡፡


ፊርማውን ለመፈረም ሊንኩን ይጫኑ; አስፈላጊውን መረጃ ከሞላችሁ በኃላ 'አስገባ' የሚለውን ትጫናላችሁ... 'አስገባ' የሚለው ቀይ የነበረው ቀለም ወደ አርንጓዴ ሲቀየር ፈረማችሁ ማለት ነው::

ለሌሎችም እንዲደርስ #Share #Forward በማድረግ ተባበሩ!

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ: ይጠብቃትም!

https://keap.page/gq193//landing-page.html#appId=gq193;siteRef=bd460600-7d31-466c-8ab1-0f3f3cbd6ed0;pageRef=edad85db-899a-4ca1-a1ba-bf5db45dda57

#Ethiopia #Children #Youth #SaveGeneration #SaveTheChildren #SaveTheYouth