AddisWalta - AW
45.2K subscribers
41.8K photos
204 videos
20 files
16.6K links
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
Download Telegram
ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ በክልሉ 4ኛውን የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር አስጀመሩ

ሰኔ 26/2014 (ዋልታ) የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ የ4ኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርኃ ግብር በኢሉ አባቦር ዞን ያዮ ጫካ ውስጥ አስጀምረዋል።

መርኃ ግብሩ "አሻራችን ለትውልዳችን ለትውልድ እንስራ ለኦሮሚያ እንትከል" በሚል መርህ ሃሳብ ነው የተካሄደው።

ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ በመርኃ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር በዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ አንድ ሰው 300 ችግኝ መትከል እንዳለበት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ባለፉት 3 ዓመታት ከ9 ቢሊየን በላይ ችግኞች መተከሉን የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አበራ ወርቁ ተናግረዋል።

በክልሉ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር በአንድ ቀን ከ4 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ለመትከል የታቀደ መሆኑም ተነግሯል።

ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችም በመርኃ ግብሩ ላይ ተገኝተው የችግኝ ተከላ አከናውነዋል።

ያዮ ጫካ በዩኔስኮ የተመዘገበ የተፈጥሮ ሀብት ሲሆን 167 ሺሕ 21 ሄክታር መሬትን ሸፍኗል።

አስቴር ጌታሁን (ከኢሉ አባቦር)

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
አፈ ጉባኤው መሻሻል የሚጠይቁ ጉዳዮች ውይይት እየተደረገባቸው ሲወጡ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ጠንካራ ምሰሶ ይሆናሉ አሉ

ሰኔ 26/2014 (ዋልታ) ሕግ ሊወጣላቸውና መሻሻል የሚጠይቁ ጉዳዮች በጥናት እየተለዩ እና ጥልቅ ውይይት እየተደረገባቸው መውጣታቸው ለሀገረ መንግሥት ግንባታው ጠንካራ ምሰሶ እንደሚሆን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ፡፡

አፈ ጉባኤው ይህን ያሉት ፌዴሬሽን ምክር ቤት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ አመራሮች ጋር በበይነ መንግሥታት የፊስካል ግንኙነት ዙሪያ ሲያካሂድ የነበረውን የምክክር መድረክ ማጠቃለያ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው፡፡

መድረኩ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የተጠናቀቀ ሲሆን የበይነ መንግሥታት የፊስካል ግንኙነት ጥናትና የፖሊሲ አቅጣጫዎች እንዲሁም ውስን ዓላማ ያላቸው የድጎማ በጀት እና የፌዴራል መሠረተ ልማት ስርጭት ፍትሐዊነት የክትትል ሥርዓትን ለማስፈጸም ረቂቅ ደንብ ለውይይት ቀርበው ግብዓት መሰጠቱን የፌዴሬሽን ምክር ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡

ሁለቱ ምክር ቤቶች በተሰጣቸው ሕገ መንግሥታዊ ስልጣንና ኃላፊነቶች መሠረት በጋራ መሥራታቸው የተጀመረውን የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ለማጎልበትና በእኩልነት ላይ የተመሠረተ አንድነት ለማሳደግ ትልቅ ድርሻ እንዳለውም አፈጉባኤው ገልጸዋል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ነገ ይጀመራል

ሰኔ 26/2014 (ዋልታ) የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ በነገው እለት በደብረብርሀን ከተማ ይጀመራል።

ስብሰባው ለ2 ቀናት የሚቆይ ሲሆን በዋናነት በሊጉ የተሰሩ ሥራዎችን በመገምገም ለቀጣይ ተግባራት አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥ ተገልጿል።

በተለይም ምግቤን ከጓሮዬ በተሰኘው መሰል የወጣቶች ንቅናቄ የተሰሩ ሥራዎችን መስክ ድረስ ወርዶ በመጎብኘት ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚደረግ ከሊጉ ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ከዚህም ጎን ለጎን ከ6 ሚሊዮን በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የ2014 የክረምት በጎ ፍቃድ ማስጀመሪያ መርኃ ግብር ይካሄዳል ተብሏል።

በተጨማሪም የብልፅግና ፓርቲ 1ኛ የወጣቶች ሊግ ጉባኤ የሚካሄድበት ቀን እና ቦታ በማእከላዊ ኮሚቴው ውይይት ተደርጎበት እንደሚወሰን የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ፕሬዝዳንት እና የጽህፈት ቤት ኃላፊ አክሊሉ ታደሰ ገልፀዋል።

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
የአፍሪካ ልማት ባንክ አህጉሪቷ በምግብ ራሷን እንድትችል የሚያደርገውን እንቅስቃሴ እንደምትደግፍ አሜሪካ ገለጸች

ሰኔ 26/2014 (ዋልታ) የአፍሪካ ልማት ባንክ አፍሪካ በምግብ እራሷን እንድትችል የምግብ ምርቷን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ እንደምትደግፍ አሜሪካ ገለጸች።

ባንኩ በአፍሪካ የሚገኙ ከ20 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ አነስተኛ ግብርና አምራቾች የአየር ንብረትን መቋቋም የሚችሉ ስንዴ፣በቆሎ፣አኩሪ አተር እና ሌሎች ዋና ዋና የሰብል ዘሮችን ማምረት እንዲችሉ እንዲሁም ለማዳበሪያና ለግብርና ሥራዎች አገልግሎት ይውል ዘንድ በግንቦት ወር 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ማጽደቁ ይታወሳል፡፡

ይህም አፍሪካ ለቀጣዮቹ አራት የምርት ወቅቶች ወደ 12 ቢሊየን ዶላር የሚያወጣ 38 ሚሊየን ቶን የምግብ እህል ምርቶችን በፍጥነት እንድታመርት ያስችላታል ተብሏል፡፡

በተለይም በሩሲያ እና ዩክሬን ግጭት ምክንያት በአህጉሪቱ ላይ እያንዣበበ ያለውን የምግብ ቀውስ ለመከላከል ባንኩ የምግብ ምርትን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳድግ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል፡፡

በቡድን 7 አባል አገራት ጉባኤ ላይ የተሳተፉት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ባይደን https://www.facebook.com/489211707826282/posts/pfbid0QKef84N4rkmJRiMtQn9H2kn2k22JmKBCuqPFwMtMNFDP9DnRhKsFKcHWNa86Gigwl/
በኮትዲቯር አስተናጋጅነት የሚካሄደው አፍሪካ ዋንጫ የጊዜ ለውጥ መደረጉ ይፋ ሆነ

ሰኔ 26/2014 (ዋልታ) በኮትዲቯር አስተናጋጅነት የሚካሄደው ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ የጊዜ ለውጥ መደረጉ ይፋ ሆነ፡፡

በሚቀጥለው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ሊካሄድ አስቀድሞ መርኃ ግብር የተያዘለት ውድድሩ በኮትዲቯር ካለው ከባድ አየር ሁኔታ ጋር ተያይዞ የቀን ለውጥ መደረጉን ካፍ አስታውቋል፡፡

የአፍሪካ እግር ካስ ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ደቡብ አፍሪካዊው ፓትሪስ ሞሴፔ ከአየር ሁኔታው ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ኃላፊነት አንወስድም ብለዋል፡፡

ይህን ተከትሎ የአፍሪካ ዋንጫ በፈረንጆቹ 2024 ጥር ወር ላይ ይከናወናል ተብሏል፡፡

ኢትዮጵያም በዚህ የአፍሪካ ዋንጫ ለመሳተፍ ብርቱ ፉክክር እያደረገች ሲሆን ምድቧን በመምራት ላይ ትገኛለች።

በተያያዘ ዜና ካፍ የአፍሪካ ሱፐር ሊግ በቀጣዩ የውድድር ዓመት ነሐሴ ወር በታንዛኒያ እንደሚደረግ ይፋ አድርጓል፡፡

በተጨማሪም ካፍ ባሳለፈው ውሳኔ የካፍ ሻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ መርኃ ግብር በደርሶ መልስ አሸናፊው እንዲለይ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ፋሲል ከነማ በጎንደር ከተማ አስተዳደር ደማቅ አቀባበል ተደረገለት

ሰኔ 26/2014 (ዋልታ) በኢትዮጵያ ቤት ኪንግ ፕሪምየር ሊግ 2ኛ ደረጃ ይዞ ያጠናቀቀው ፋሲል ከነማ በጎንደር ከተማ አስተዳደር ደማቅ አቀባበል ተደረገለት፡፡

አምና የሊጉ ሻምፒዮን የነበረውና በዚህ የውድር ዓመት ከሁለተኛው የውድድር አጋማሽ ጀምሮ ምርጥ ፉክክር ሲያደርግ የቆየው ፋሲል ከነማ በቅዱስ ጊዮርጊስ ተበልጦ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡

በሊጉ ባደረጋቸው 30 ጨዋታዎች 61 ነጥብ በመያዝ ያጠናቀቁት አፄዎቹ ዛሬ ወደ ጎንደር ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡

ክለቡ በውድድር ዘመኑ ላስመዘገበው ውጤትም የከተማ አስተዳደሩ 7 ሚሊየን 462 ሺሕ 500 ብር፣ ከክለቡ 2 ሚሊየን 487 ሺሕ 500 ብር በድምሩ 9 ሚሊየን 950 ሺሕ 500 ብር ለክለቡ ተጫዋቾችና ለአሰልጣኞች እንዲሁም ለአጠቃላይ ሰራተኞችና የቦርድ አመራሮች የማበረታች ሽልማት ተበርክቷል።

በአቀባበሉ የከተማዋ ተቀዳሚ ከንቲባ ዘውዱ ማለደና ሌሎች የጎንደር ከተማ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል፡፡

ክለቡ በቀጣዩ የውድድር ዓመት በአፍሪካ መድረክ በክለቦች የኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ጨዋታ ላይ ኢትዮጵያን የሚወክል ይሆናልም ነው የተባለው፡፡

በሀብታሙ ገደቤ

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
የማታ 1፡00 ዜና በቀጥታ ከዋልታ ቴቪ ሰኔ 26/2014
https://fb.watch/e1tPv7s0cv/
በሊጉ ጨዋታዎች ላይ የተፈጠሩ ክስተቶችን ተከተሎ ለጨዋታ ታዛቢዎች፣ ዳኞችና የቡድን መሪዎች ጥሪ ተደረገ

ሰኔ 26/2014 (ዋልታ) ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ላይ የተፈጠሩ ክስተቶችን ተከተሎ ለጨዋታ ታዛቢዎች፣ ዳኞችና የቡድን መሪዎች ጥሪ ተደርጓል።

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ሥነ ሥርዓት ኮሚቴ ዛሬ ባደረገው ስብሰባ የተደረጉ ፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያዎች ከዳኞች እና ከታዛቢዎች የቀረቡለትን የዲሲፕሊን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

በተጫዋቾች ዳንኤል ተሾመ (አዲስ አበባ ከተማ)፣ አብዱልባሲጥ ከማል (ሃዋሳ ከተማ) እና ጀማል ጣሰው (አዳማ ከተማ) በ5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ የተመለከቱ 1 ጨዋታ እንዲታገዱና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት 1 ሺሕ 500 ብር እንዲከፍሉ ተወስኗል።

በ30ኛ ሳምንት በተደረጉ ጨዋታዎች ላይ የተፈጠሩ ክስተቶችን ተከተሎ ለጨዋታ ታዛቢዎች፣ ዳኞችና የቡድን መሪዎች የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ውድድርና ሥነ ሥርዓት ኮሚቴ ለማነጋገር በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክሲዮን ማኅበር ጽ/ቤት እንዲገኙ ጥሪ ተላልፏል።

በዚህም ለሦስት የጨዋታ ታዛቢዎች ሻለቃ በልሁ ኃይለማሪያም፣ ሰላሙ በቀለ እና አበጋዝ ነብየልዑል ሲሆን ከዳኞች ለኢንተርናሽናል ዳኛ ኃይለየሱስ ባዘዘው (ፒኤችዲ)፣ ለኢንተርናሽናል ዳኛ አሸብር ሰቦቃ፣ ለፌዴራል ዳኛ ኤፍሬም ደበሌ፣ ለፌዴራል ዳኛ ባህሩ ተካ ለፌዴራል ዳኛዮናስ ካሳሁን እና ለፌዴራል ዳኛ እያሱ ፈንቴ ጥሪ ቀርቧል።

https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/photos/a.489214534492666/5571310619616340/?type=3&app=fbl
በሶማሌ ክልል በሙስና በተጠረጠሩ 168 የመንግሥት ሰራተኞች ላይ ክስ ተመሰረተ

ሰኔ 26/2014 (ዋልታ) የሶማሌ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊነትን ለግል ጥቅም በማዋልና በሙስና ወንጀል በተጠረጠሩ 168 የመንግሥት ሰራተኞች ላይ ክስ መሰረተ፡፡

የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አህመድ ሃጂ እንደገለጹት በገቢ ማሰባሰብ ሥራ ላይ የተሰማሩ ሰራተኞች ላይ በተደረገ የኦዲት ምርመራ 93 ሚሊየን ብር ጉድለት እንደተገኘ የሶማሌ ክልል ጠቃላይ ኦዲት ጽ/ቤት ለአቃቤ ህግ በላከው ሪፖርት አረጋግጧል። ይህን ተከትሎም በገንዘብ ምዝበራው ተሳትፎ አላቸው በሚል በተጠረጠሩ 168 የመንግሥት ሠራተኞች ላይ ክስ ተመስርቷል፡፡

ቢሮው ከፖሊስ ጋር በመተባበር በወሰደው እርምጃም እስካሁን ከተለያዩ ግለሰቦች 15 ሚሊየን ብር ተመላሸ ሆኖ ወደ መንግሥት ካዝና መግባቱን ጠቁመዋል።

በተመሳሳይ የሶማሌ ክልል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በሶማሌ ክልል ንግድና ትራንስፖርት ጽ/ቤት ሰራተኛ ሆነው የመንግሥትና የሕዝብ ሃብትን ለግል መጠቀሚያ በማድረግና በሙስና በተጠረጠሩ 14 ሠራተኞች ላይ ክስ የመሠረተ ሲሆን ከተከሳሾቹ መካከል ሁለቱ ዳይሬክተሮች መሆናቸውን ኃላፊው ገልፀዋል።

ከነዚህ 14 ግለሰቦች መካከል 4ቱ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ የቀጠለ ሲሆን ቀሪዎቹን ለህግ ለማቅረብ ክትትል እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው ከተጠርጣሪዎቹ ጋር በግብረአብረነት ተሳትፎ እንዳላቸው በተጠረጠሩ 17 ነጋዴዎች ላይም ክስ መመስረቱን ተናግረዋል።
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/photos/a.489214534492666/5571417646272304/?type=3&app=fbl
የኢትዮጵያ እና ሱዳንን ሕዝቦች ሰላማዊ ግንኙነት ለማጠናከር ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት ይገባል ተባለ

ሰኔ 26/2014 (ዋልታ) የኢትዮጵያን እና የሱዳንን ሕዝቦች ሰላማዊ ግንኙነት ለማጠናከር ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት እንደሚገባ በሱዳን የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ ገለጹ፡፡

አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ ከሱዳን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ደፋኣላ አልሃጅ ጋር በኢትዮጵያና በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም በሁለቱ አገራት ሕዝቦች መካካል ያለው ግንኙነት ለዘመናት የዘለቀና በመልክዓ ምድር፣ ባህል፣ ታሪክ እና ሃይማኖት የተሳሰረ መሆኑን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ አውስተዋል።

በሁለቱ መንግሥታት መካከል ልዩነቶች ቢከሰቱም እንኳ ዘላቂና ስትራቴጂካዊ ጥቅሞቻችንን ግምት ውስጥ በማስገባት በሰከነና በሰላማዊ መንገድ ልዩነቶችን ለመፍታት መስራት አስፈላጊ ነው ሲሉ አስረድተዋል።

አምባሳደር ደፋኣላ አልሃጅ በበኩላቸው የሁለቱን አገራት ሕዝቦች ሰላማዊ ግንኙነት ለማጠናከር በሁለቱ መንግሥታት መካካል የሚነሱ ልዩነቶችን በውይይትና በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሱዳን ዝግጁ ናት ማለታቸውን በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ቢሮው ከመንግሥት የተሰጠውን መመሪያና ደንብ የጣሱ 8 የነዳጅ ቦቴዎችን ወረሰ

ሰኔ 26/2014 (ዋልታ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ከመንግሥት የተሰጠውን መመሪያና ደንብ ችላ በማለት ከሕግ ውጪ ነዳጅ የጫኑ ስምንት የነዳጅ ቦቴዎች መውረሱን አስታወቀ፡፡

ሆን ብለው የነዳጅ እጥረት እንዲከሰትና ከመንግሥት የተሰጠውን መመሪያና ደንብ ችላ በማለት ከሕግ ውጪ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች ወደ ከተማ እንዳይገቡ ያደረጉ ስምንት የነዳጅ ካምፓኒዎች ቦቴዎች በዛሬው እለት በፀጥታ ኃይሎችና በኅብረተሰቡ ጥቆማ ተወርሰዋል፡፡

የተወረሰው ነዳጅም በነዳጅ ማደያዎች በኩል እንዲከፋፈል ማድረጉን ቢሮው አስታውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ምክትል ኃላፊ መስፍን አሰፋ ሕግ አክብረው በማይሰሩና በትክክል ስራቸውን በማይወጡ የነዳጅ ካምፓኒዎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ማለታቸውን ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
ኢዜማ ብርሃኑ ነጋን (ፕ/ር) በድጋሚ የፓርቲው መሪ አደርጎ መረጠ

ሰኔ 27/2014 (ዋልታ) የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ሰኔ 26 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ አመሻሽ ባካሄደው አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤው በየዘርፉ ተፎካካሪ እጩዎች ቀርበው የምረጡኝ ቅስቀሳ ካደረጉ በኋላ አሸናፊዎቹን እኩለ ሌሊት ገደማ አሳውቋል፡፡

በዚሁ መሰረት ፓርቲው ብርሀኑ ነጋን (ፕ/ር) መሪ እና ዮሐንስ መኮንንን ምክትል መሪ አድርጎ መርጧል፡፡

ጫኔ ከበደ (ዶ/ር) እና አማኑኤል ኤርሞ (ዶ/ር) ደግሞ የፓርቲው ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል፡፡

ኢዜማ አበበ አካሉን ዋና ፀሀፊ አድርጎ የመረጠ ሲሆን በሚስጥር በተካሄደው የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት በሌሎችም ዘርፎች ፓርቲውን የሚመሩ አባላትን ጭምር መርጦ መሰየሙን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል፡፡

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW