ኢትዮጵያዊ ወጎች #Ethiopian
1.49K subscribers
314 photos
3 videos
18 files
50 links
Download Telegram
## ዓድዋ በባለቅኔው እይታ ###

ዋ! ..... ያቺ ዓድዋ

ዋ! ...
ዓድዋ ሩቅዋ
የአለት ምሰሶ አድማስ ጥግዋ
ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ
ዓድዋ.....
ባንቺ ብቻ ሕልውና
በትዝታሽ ብፅዕና
በመስዋዕት ክንድሽ ዜና
አበው ታደሙ እንደገና
ዋ!
ዓድዋ የዘር ዐፅመ ርስትዋ
የደም ትቢያ መቀነትዋ
በሞት ከባርነት ሥርየት
በደም በነፃነት ስለት
አበው የተሰውብሽ ለት
ዓድዋ
የኩሩ ትውልድ ቅርስዋ
የኢትዮጵያነት ምስክርዋ
ዓድዋ
የኩሩ ደም ባንቺ ጽዋ
ታድማ በመዘንበልዋ
ዐፅምሽ በትንሳኤ ንፋስ
ደምሽ በነፃነት ሕዋስ
ሲቀሰቀስ ትንሳኤዋ
ተግ ሲል ሲንር ትቢያዋ
ብር ትር ሲል ጥሪዋ
ድው እልም ሲል ጋሻዋ
ሲያስተጋባ ከበሮዋ
ሲያስገመግም ዳኘው መድፍዋ
ያባ መቻል ያባ ዳኘው
ያባ ነፍሶ ያባ ቃኘው
ያባ በለው በለው ሲለው
በለው በለው በለው በለው
ዋ! ...... ዓድዋ .....
ያንቺን ፅዋ ያንቺን አይጣል
ማስቻል ያለው አባ መቻል
በዳኘው ልብ በአባ መላው
በገበየሁ በአባ ጎራው
በአባ ነፍሶ በአባ ቃኘው
በለው ብሎ በለው በለው
ዋ! ...... ዓድዋ .....
ዓድዋ የትናንትናዋ
ይኸው ባንቺ ሕልውና
በትዝታሽ ብፅዕና
በመስዋዕት ክንድሽ ዝና
በነፃነት ቅርስሽ ዜና
አበው ተነሱ እንደገና
....... ዋ! ........ ያቺ ዓድዋ
ዓድዋ ሩቅዋ
የአለት ምሰሶ አድማስ ጥግዋ
ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ
ዓድዋ .......

© ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን
የካቲት - ፲፱፻፷፬ - ዓድዋ

#የጥቁር_ህዝብ_ኩራት
#ዓድዋ_123
#የኢትዮጵያውያን_ድል
#VictoryofAdwa
#Ethiopia

@Simetin_Begitim
@Simetin_Begitim
የአድዋ አዋጅ እና እምዬ ምንሊክ ብልሀት

#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ

"የዳግማዊ ምኒልክ የክተት አዋጅ ከወራሪዎቹ እንቅስቃሴ አንፃር ከተጠበቀበት ወቅት ዘግይቷል፡፡ ይህም በአፍሪካና አውሮፓ ሀገሮች አይን ምንሊክን እንደ ፈሪ እንዲታዩ አድርጎ ነበር ይላል" ራይሞን ጆንስ የአድዋ ጦርነት በሚለው መፅሀፉ፡፡ ፀሀፊው ሲቀጥል "የመሪ ብልህነት የሚለካው ቸኩሎ በመወሰኑ ሳይሆንበወቅቱ ያሉትን አመቺ ሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ሲያሳልፍ ነው ይላል፡፡
የክተት አዋጁ በራሱ በወቅቱ ኢትዮጵያ የነበረችበትን የፈተና ጊዜ ማለፍንና የመረጋጋት ዘመን መምጣቱን ገላጭ ከመሆኑም በላይ፤ ህዝቡ ከሃይማኖት፣ ከዘርና ግዛት ማስፋፋት ፍጭት በመውጣት ስለ አንድ ሀገሩ ደህንነት በጋራ የሚቆም እንደነበረ ያረጋግጣል።

" እግዚአብሔር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ፣ አገር አስፍቶ አኖረኝ" ሲሉ ከአድዋ በፊት ጠንካራ የውጭ ጠላት አልነበረምና ጦርነት በሌለበት ሀገር እርጋታ ላይ ሆና አስተዳደሯን እያደረጀች እንደነበረ ይነግረናል።

" አሁንም አገር የሚያጠፋ፥ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት እግዚአብሔር የወሰነልንን ባህር አልፎ መጥቷል። እኔም ያገሬን ከብት ማለቅ የሰውንም መድከም አይቼ እስካሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈ እንደ ፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር።"

ይህ ንግርት በወቅቱ ኢትዮጵያ የነበረችበትን የመከራ ዘመን "ክፉ ቀን" ደግመን እንድንመረምር ያደርገናል። በከ1881 ዓ.ም ጀምሮ የነበረው በኢጣሊያኖች አማካኝነት ወደ ሀገር የገባው የከብት በሽታ ለአራት አመታት ህዝቡን ከብቱን ጎድቶ ነበር። ረሀብ በመፅናቱ እናት ልጀቿን የበላችበት ክፉ ዘመን ነበር። እናም የዓድዋ ጦርነት ለምን ዘገየ ሲባል ራሱ አዋጁ ይነግረናል " የሰውን መድከም የከብቱን ማለቅ አይቼ እስካሁን ዝም ብለው" ይህ ሀሳብ ከላይ ራይሞን ጆንስ ከጠቀሰው ጋር የሚስማማ ነው፡፡

እምዬ በጥሪያቸው " ማርያምን አልምርህም! ለዚህ አማላጅ የለኝም " ብለዋል። ግን ሀገሬው በሙሉ ሃይማኖቱን አስቀድሞ በእምነቴ አልተጠራሁም ብሎ ሀገሩን ከመታደግ አልቀረም። ንጉሱን ተከትሎ ከንጉሱ ጋር ተዋደቀ እንጂ።

ለዛ ነው እምዬ ከምንም በላይ ሀገር እንደሚቀድም አሳይተው በአንድነት የመምራት ብቃት ነበራቸው የሚያሰኘው።

ክብር ይሁን!

#የጥቁር_ህዝብ_ኩራት
#ዓድዋ_123
#የኢትዮጵያውያን_ድል
#VictoryofAdwa
#Ethiopia

@Simetin_Begitim
@Simetin_Begitim