ኢትዮጵያዊ ወጎች #Ethiopian
1.51K subscribers
314 photos
3 videos
18 files
50 links
Download Telegram
እንኳን ለ 1441ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ውድ የቻናላችን የእስልምና እምነት ተከታዮች
በዓሉ የሠላም እና የጤና እንዲሆንላችሁ እንመኛለን ፡፡

የጤና ባለሙያዎችን ምክር በመከተል የኮሮና ቫይረስን እንዲከላከሉ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።
#We wish you a Happy Eid
°°°°°°°°°°°°°
የሰፈራችን አባቶች የገዙት በሬ አንድ አይን አልነበረውም!
የት ዘምቶ እንደሆነ እንጃ!
እንደ ጭቃ ሹም ታጅቦ መጣ።
አረማመዱ መቼም የጤና አልነበረም። ልክ የሰፈራችን የቆሻሻ
ገንዳ አጠገብ ሲደርስ ደነበረ!
ተፈነጣጠረ!
አባቶቻችን እንደ ዝምብ መንጋ ዝዝዝዝ..ብለው ተበተኑ!
" ያዘው! ያዘው! "
ከወኔ ውጪ ሰውነት የሌላቸው ጋሽ ብሩ ቁልቁል የሚንደረደረውን
በሬ በሩጫ ተከተሉት
...ግን ተሳሳቱ--- ፈጠኑ....በጣም!
በሬው ቀጥ ብሎ ሲቆም ጋሽ ብሩ ፍሬናቸውን በጥሰው እግሩ ስር
እንደ ሊስትሮ.....
በሬው በቀኟ ዐይኑ እንደ መሽኮርመም አለና!
በቀንዱ ዘገናቸው! ( የምሬን ነው )
እንደ ጀላቲ ቀንዱ ጫፍ ላይ ሰክቷቸው ሲታይ የፈረንጅ አጋዘን
ይመስል ነበር።
ዘቅዘቅ ሲሉ፡ ነጯ ኮፍያ ጠብ አለች!
" በህግ አምላክ! "....አሉ አየር ላይ ( ማንን ይሆን? )
በሬው ጋሽ ብሩን አንጠልጥሎ ወደገንዳው ተመለሰና ገንዳው
ውስጥ ጨመራቸው!( አስቀመጣቸው ልበል? )
ተረኛ የሚዘገን ሲፈልግ፡ ሰዉ ተተራመሰ!
ዞሮ ዘሎ ሲመጣ ጋሽ ብሩ ከገንዳው ብቅ አሉ!
አልጋ ስር የተረሳ ጫማ መስለው..
" ኮፍያዬን አላያችሁም? "
" አላየንም "
" ያችኋትናኮ አቀብሉኝማ "
" ሌላ ቀን ይውሰዷት "....በዚያ ላይ
" ቢወጋንስ? "
" እኔ አባታችሁ እንዴት ልውጣ ታዲያ? "
እንዳይወጡ ቆሟል ፊት ለፊት
" ኧረ ጠነባሁ ጎበዝ "
መቼስ ብዙ ስቀናል ያኔ። በስንት መከራ ተሸነፈ!
ታርዶም ጣጠኛ ነበር
የታረደ ቀን ጠዋት ቅርጫው ላይ ጫጫታ ይሰማል
ጨጓራው ተሰረቀ!
ያው ከሮቤል ውጪ መቼም ማንም አይሆንም!
የነሮቢ በር በሃይል ተንኳኳ!...ሮቢ ከፈተ
" ጨጓራውን መልስ! "
" ኧረ ጋሼ! የምን ጨጓራ? "
" ዛሬ ፊኛህን ተሰናበት! ልቆምበት ነው "
" እኔ አላየሁምኮ "
" ምንድነው በመዘፍዘፊያው ያስቀመጥከው "
" የባቢ ሽንት ጨርቅ ነው "
" እያጠብክለት? "
" አዎ "
" በፈርስ ነው የምታለቀልቀው? "

Fikre Ze Bhere Ethiopia
#የመልስሽ #ጥያቄ

#እኔ #ምልሽ
የእንባችን ገንቦ ~ ሳይሰበር በፊት
ይፈስ ነበር አይደል ~ በሳቃችን ግፊት
የተፈጥሮስ ሂደት ~ እንዲህ ሳይጓደል
ከልብ እየሳቁ ~ ማልቀስ ነበር አይደል ?

#እኮ
#እኛ #እኮ #ነን
ሀዘንን በደስታ _ እያነሳን ልንጥል
ስሜታችን ቆርጠን _ ስሌት ልንቀጥል
በአንድ ወገን ስለነው ~የተፈጥሮን መቀስ
በየተራ ሆኗል ~ መሳቅና ማልቀስ
===||===
ከሙሉቀን ሰ•
ለፎቶ የተዋስናቸው የልደት ለስላሳዎች ከኛ በላይ celebrate
ይደረጉ ነበር....
የዘንድሮው ወላጅ፡
" ኧረ ቀስ ልጆች እንዳትደፉት! "
ያኔስ?
" ቀስ! ዋ! እንዳትከፍቱት! በሰንበቱ አትነጅሱኝ".
.....ተመላሽ ነዋ!.....
ሙስጤ በሩን ያንኳኳል ( ባለሱቁ )
ሲከፈት፡
" መልሱንጂ "
" ቆይ አዩ ይምጣ! "....አዩ ፎቶ አንሺ ነው ...የሰፈራችን።
ሙስጤ አምስት ኮካና ምሪንዳ አውሶን፡ የጌቱን ልደት አድምቀን
ልንመልስለት ነበር ውሉ...
" አስር ደቂቃ ብቻ! "
" ወላሂ! ካሁን በኋላ ግን አላውሳችሁም "
***
አንድ ቀን ሃያ ብር ወድቆ አገኘሁ! አቤት ደስታዬ!
ሰው ፈንክቼ ካሳ መክፈል ሁሉ አማረኝ!
ቀጥታ ሙጤ ጋር ሄድኩ
" ሙስጤ እስኪ ሁለት ምሪንዳ ስጠኝ! "....ለራሴ ነውኮ
" ፍቅርሻ ለልደት አውሸዋለሁ! "
.....እርሜን ገንዘብ ብይዝ!?.......
" በቃ ተወው! ዳኜ ጋር እሄዳለሁ " ስለው፡
" ቆይንጂ! ካላመንከኝ ና ይዤህ ልሂድ " ብሎ ወንድሙን
'መጣሁ አደራ' ብሎት አብረን ሄድን
ልደቱ የጩና ነበር። ኮካው አልተከፈተም። አዩ ፎቶ ያነሳል።
" ያውልህ! አንዱን አንስተህ ጠጣ! " አለኝ
......አዝማሪ በሰው ሰርግ ይዳራል ይልሃል ይሄ ነው!....
ተንደርድሬ ብድግ ላደርግ ስል፡ የጩና አባት፡ አንገቴን እንደ
ብርሌ ሲጥ አድርገው፡
" እናትህ ወልዳሃለች ዛሬ! "...አሉኝ
ሙስጤ፡ መጥቶ አረጋጋቸውና
" ገዝቶታል ጋሼ! "
" እና!? "
" ልጠጣ? " አልኩ ጣልቃ ቀብቼ
" ልደቱኮ የጩና ነው! እሷ ሳትጠጣ በሰው ልደት እዚህ
ሊጨልጥ? "
መቼስ የልደቴ ቀን ባልጠጣ የጩና ላይ ይመርብኝንጂ!
ጩና እየተቁለጨለጨች፡ እኔ የሷን ምሪንዳ ፉት እያልኩ
አስቡት!......( መቃብሬ ላይ ትቆማለች? )
በነገራችን ላይ ጨዋታውን አልኩንጂ እኛ ሰፈር ልደታቸውን
የሚያከብሩት ጥቂቶቹ ናቸው
ሶስት ወይም አራት ይሆናሉ። ሁለቱ በቋሚነት የሚያከብሩ
ደምበኞች ሲሆኑ፡ ሌሎቹ ሲኖር የሚደረግላቸው ናቸው።
ታዲያ የኛ የራሳችን ልደት እስኪመስለን እናከብርላቸው ነበር።
የኛን ሳናውቅ የነሱን!
የሆነው ሆኖ ሃያ ብሬን ሆጭ አድርጌ ጩና እና ሌሎቹን
ለለስላሳው ከፍዬ አንበሻበሽኳቸው!
አባቷም ያን ያህል አላወጡ
" ፍቅርሻ! በሰፈሯ ለመጀመሪያ ጊዜ የልደት ኮካ አስከፈተች!
".......ብሏል ሃበሻ!

Fikre Ze bhere Ethiopia
መርዶ
[በዕውቀቱ ሥዩም]
____________
ተምትም አሻግሬ የሚባል ጓደኛ ነበረኝ ። አይ ተምትም አሻግሬ !
ባሰብሁት ቁጥር ሳቄ ዝም ብሎ ይመጣል ።
ተምትም ንግግር በማስረዘም ተወዳዳሪ የለውም ። ለምሳሌ
አብረን አምሸተን ስንለያይ እኔ ''ቻው!'' እለዋለሁ። እሱ ግን
'' ....ደህና አምሸተህ ሌሊቱን በሰላም ታሳልፍ ዘንድ
እመኝልሃለሁ!'' ይላል ።
ቁርስ ልንበላ ስናዝዝ '' ቋንጣ ፍርፍር!'' ብሎ እንዳይገላገል ''
''እስቲ እባክሽ የኔ እመቤት ፣ ሽንኩርት ሳይታይ ፣አንድ ጥሩ የሆነ
ከቋንጣ የተሰራ የእንጀራ ና የልዩ ልዩ ነገሮች ፍርፍር አምጭልኝ
....'' ይላል ።
ተምትም እና እኔ አንድ ቀን የጓደኛችን የደመቀ ባይከዳኝን
ወንድም ሞት ሰማን። መርዶውን ለመናገር የታጨን ሁለታችን
ነበር። ''እኔ ቀስ ብዬ ብነግረው ይሻላል !....አንተ ታስረዝማለህ!''
አልኩት። እሱ ግን የንግግር ሱስ ስላለበት ተቃወመኝ።
''ምን ነካህ!....መርዶ እንዲህ ቀላል ነገር ነውንዴ ?....እኔ ነኝ
በዘዴ ልነግረው የሚገባ ....ይልቅ ራሱን የሳተ እንደሁ አንተ
ትደግፈዋለህ!'' አለኝ ።
ከብዙ ጭቅጭቅ በኃላ እሱ አሸነፈኝ ። በማግስቱ ሌሊት ወደ
ደመቀ ቤት ስንሄድ ''አደራ እንግዲህ እንዳታንዛዛው....ወንድምህ
በመኪና አደጋ ስላረፈ ርምህን አውጣ ! ማለት ብቻ ነው'' አልኩት
።።
እሺ ብሎኝ ገባን።
ደመቀ ከእንቅልፋ ተነስቶ በር ከፈተልን በኃላ {ምነው በደህና?}
አለን ። ምልክት ሳሳየው ተምትም ንግግሩን ለቀቀው ''ውድ
የተከበርከው ወንድማችን ደመቀ ባይከዳኝ....ወንድምህ ከሁለት
ቀናት በፊት እናቱን ለመጠየቅ መኪናውን እየነዳ መውጣቱን
ሳታስታውስ የምትቀር አይመስለኝም....ያን ቀን ከሌሎች ቀን
የከበደ ቀን ነበር ....ሰማዩ ርጉዝ አህያ መስሏል ።ወንድምህ
ምነው ዛሬ ቀፈፈኝ እያለ ለራሱ በመናገር መኪናውን በአባይ
ጎዳና ማሾር ጀመረ ...ጸጥ ያለ መንገድ ነበረ ...ምነው የሆነ
መልአክ ተመለስ ብሎ ሹክ ባለው !...ዋ! .....ጎደሎ ቀን ! ዋ
የተሰበረ ዕድል ....ምንኛ ያሳዝናል! ....በአባይ ሽለቆ ውስጥ
ሲገባ የመኪናውን ፍጥነት አልቀነሰም ፤ እናም ወደ ግራ
እዞራለሁ ሲል መኪናው እንደ ኳስ ነጠረች !... ከዚያም ሙሽራ
ሙሽሪትን እንደሚስም ሁሉ መኪናዋ ባቅራቢያው ካለ ቋጥኝ ጋር
ተሳሳመች....ግው! ጓ!
ወንድምህ ! ያ! ቅን ወንድምህ ከዚህ የጨቀየ ዓለም ወደ
ብርሃናዊውና የማይከስመው ዓለም የተሸጋገረው በዚህ ጊዜ
ነው !'' አለና ትንፋሹን ዋጠ።
ደመቀ ግን '' አልገባኝም !'' ብሎ ወደ እኔ ተመለከተ ።
'' ወንድምህ አርፏል !'' አልኩት በፍጥነት ። እሱም በፍጥነት
ወደቀ ።
#stayHome
#Staysafe
#Fact
ኢትዮጵያ” ማለት በአይሮግሊፊክ አትኦፕቢያ “የበላይኛው
የእውነት አገር” ማለት ነው፡፡
“ሳባ” ማለት “የመንፈስ ልጅ” ማለት ነው፡፡
“ጋላ” ማለት ለቧልት እንደሚባለው “ሃይማኖት የሌለው” ማለት
ሳሆን ካራ “የእግዚአብሔር ፀሐይ ፋና” እንደማለት ነው፡፡
“ዐማራ” ማለት በሻዕቢያ ቧልት እንደተባለው “ወፈፌ” ወይም
“ፉዞ” ማለት ሳይሆን “ዓም ሀራ” ወይም “የካም ሰራዊት ፀሐይ”
እንደማለት ነው፡፡
“ሃማ ሴን” “የካምን ወገን ዝርያ” እንደማለት ነው፡፡
“አጋሜ” ማለት በቧልት እንደሚባለው “ለማኝ” ወይም “ቆሻሻ”
ማለት ሳይሆን “አጋ ሃሜ” “ታላቅ የካም ወገን” እንደማለት ነው፡፡
“እግዚአብሔር” ማለት “እግ-ዘ-አብሔር” “ታላቁ የምድር አባት”
ማለት መሆኑን፣ “ጋዳ” ማለት “ካ አዳ” “የእግዚአብሄር ሥርዓት”
ማለት ነው ፡፡
ፀጋዬ ገ/መድህን
ምንጭ፡- ጢቢያ መፅሄት ቅጽ 5፣ ቁጥር 11፣ 1990
#ከFb የተመነተፈ
መልካም ቀን
ʟօʋɛʀs ɛʍքɨʀɛ :
"እኔ_ደግሞ …."
(አሌክስ አብርሃም)

ምንድነው እንደዚህ - ፊቴን በብረሃን
ከንፈሬን በውብ ሳቅ - የሚያጥለቀልቀው፣
ምንድነው ከልቤ - ኮለል ያለ ሰላም - በጧት የሚፈልቀው?።
እያልኩ አስባለሁ ……

እኔ ደግሞ …..
ምንድነው ሰው ሁሉ- ነጫጭ ክንፍ አብቅሎ - መ,ላክ የመሰለው፣
ምንስ ነው ሰማዩ - እንዲህ ተጠቅልሎ -
በጀ የምይዘው - መሃረም ያከለው።

ኧረ ምን ታምር ነው - መሬት መዞር ትታ - በፎይታ ያቆማት፣
ምንድነው ጨረቃን - ከሰማይ አወርዶ - ምድር -ያሳረፋት?።
እያልኩ አስባለሁ

እኔ ደግሞ …..
የጠሉኝን ሁሉ - ድንገት የመውደዴ፣
መሬቱን ለቅቄ - ባየር ላይ መንጎዴ።

ምንድነው ሚስጥሩ-ቆይ ውስጤን ምን ነካው፣
አለም እንዲህ ጠቦ - በርምጃ ሚለካው።

ውቂያኖስ በፍኘ - ተጨልፎ የሚደርቅ፣
ተራራው በክንዴ - ተጎሽሞ ሚደቅ።

ማነው በመንገዴ - ሳልፍ እልል የሚለው አበባ ነስንሶ፣
ማነው ግማሽ ልቤን - ሸርፎ የወሰደው -በትልቁ ቆርሶ?።
ኧረ ምን ታምር ነው ?
እያልኩ አስባለሁ

እኔ ደግሞ …..
መንገዳኛው ሁሉ - የተከፋ ፊቱን -
በማን ተነጠቀ፣
ከጨፍጋጋ ፊቶች - የዚህ አይነት ብርሃን - እንዴት ፈነጠቀ።

ሚሊየን ህፃናት - ቀልብ በሚነሳ -
ስርቅርቅ ድምፃቸው፣
የት ቢዘምሩ ነው - ልቤ ሚሰማቸው።

በምን ተአምር ነው - ዛፎች የሚያረግዱት፣
በምን ጉድ አስማት ነው - የሰማይ ከዋክብት
ቁልቁል የሚበሩት።
እያልኩ አስባለሁ ….

እኔ ደግሞ ….
ቤሳ ቤስቲን ፍራንክ - ኪሴ ሳይጨመር፣
አመት የለበስኩት - ልብሴ ሳይቀየር።

የዘወትር ጉርሴ - ጣሙ ሳይነካ፣
እኔነት እኔ ውስጥ - ተቀይሯል ለካ።

እኮ በምን ምክንያት - እኔ ተቀየርኩኝ፣
እንዴት እኔ ነኝ ስል - እኔ ሌላ ሆንኩኝ።
እያልኩ አስባለሁ ……..
ለ ካ ስ ……………………..አፍቅሬሽ ነው!!!
#StayHome
#StaySafe
ሰሞኑን በአንዳንድ የግል ችግር ምክንያት ጥያቄዎችን እና መረጃዎችን አዘጋጅተን ማቅረቦ አልቻልንም ለዚህም ይቅርታ እንጠይቃለን በቅርቡ ከSurprise Gift ጋር እንመለሳለን እስከዛው አብሮነትዎ አይለየን ፡፡ መልካም ጊዜ!!

#Share these link to your friends
https://t.me/joinchat/AAAAAE1DeWswU2W9sUd-rA
#Attention 🔔🔔🔔
ከፍተኛ ጥንቄቄ ይደረግ!

- በአዲስ አበባ ያለው ሁኔታ ለይቶለት ታውቋል ፤ የቫይረሱ ስርጭት በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ ነውና ከመደናገጥ #መጠንቀቅ ያዋጣል።

- በክልል ከተሞች ስርጭቱ አነስተኛ ነው በሚል መዘናጋት ተፈጥሮ ከፍተኛ ችግር ውስጥ እንዳይከተን ሊሰራ ይገባል። ከአዲስ አበባ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ አለመቋረጡን ልብ እንበል!

- ኮቪድ-19 በክልል ከተሞች ሳይታወቅ ውስጥ ውስጡን በከፍተኛ ሁኔታ ከተሰራጨ በኃላ ለመቆጣጠር ፍፁም ከባድ ይሆናልና ሁሉም አካል ከወዲሁ ኃላፊነቱን ይወጣ።

በበሽታው መያዛችን ዕለት-ተዕለት በምናደርገው እያንዳንዱ እንቅስቃሴ የሚወሰን መሆኑን በማስታወስ አራቱን የ’’መ’’ ህጎች (መታጠብ፣ መሸፈን፣ መራራቅ፣ መቆየት) ተግባራዊ እናድርግ!
#ዝም #ዝም

ሆድ ከሀገር ይሰፋል~ በሚሉባት ሀገር
አፍ ከአለም መስፋቱን ~ለማን እንናገር ?
ለማን እንናገር ~ እኮ ለማ እንማው
አፍ ባጋለው ሐገር~ምጣድ ነው
ሚሰማው
#ሰማ #ሰማ #ብለን
በቶሎ ተጋግረን ~ በጊዜ እንዳንወጣ
በሰማ ምጣድ ላይ ~ የሚያሰፋ መጣ
የሚያሰፋው መጣ ~ሊጡን አንጠልጥሎ
ማልዶ ሊማግድህ ~ ነፃ ላውጣህ ብሎ
ተናገር ይልሀል ~ አስከብር መብትህን
እንዳሻህ ተጠቀም ~ ሰብአዊነትህን
#እኔ ግን #እላለሁ
በንግግር ብቃት ~ እልፎች ቢጀግኑም
አንድ ሺህ ምላሶች ~አንድ ጆሮ አይሆኑም
በምላስ ተስቦ ~ ከሰነባበተ
ጆሮን ይከልላል ~ አፍ ከተከፈተ
#እኔ #ጠይቃለሁ
የወል ጥያቄህ ላይ
ያለ ሀሳብ ተኝተው ~ ሠው ለሚያንተርሱ
መናገር አይደል ወይ ~ ዝም ማለት ራሱ
#እኔ #ሞግታለሁ
ሐሳብን በመግለፅ ~ በመናገር አለም
ዝም የማለት መብቱን~የሚያስከብር የለም
#እኔ #እጠቁማለሁ
በነፃነት ጥላ ~ ግብሩ የተከለለ
በመናገር መብት ውስጥ~ዝም የማለት አለ
===||===
ከሙሉቀን ሰ•
#ቅንጭብጭብ_ኢትዮጵያ

፬ እርምጃ
°°°°°°°°°°
[ናዝሬት]

ከቦሌ እስከ ማርያም አራት እርምጃ ነው
ስሰክር ስሰክር ወይ ሲለኝ ድንግር ግር
እኔ የምራመደው።
እህ በይኝ እና ልንገርሽ አንቺዬ ስሚኝ ባዛኝቱ
ባይጥምም አይመርም ያፍቃሪ እውነቱ
የናፍቆት ዝለቱ
እህ በይ እህ በይ እህ በይ በማርያም ሰሚው እውነታዬን
ስሰክር ስከፋ የምረግጠውን ሃቅ የውነት እርምጃዬን

በጎዳናው መሃል በድንጋዩ ንጣፉ ካብታሞቹ ሰፈር
ስኔድ ትዝ ካለሽ ወሬ ስንረሳ ወሬ ስንጀምር
ምነዋ አንቺዬ
እንደውም ፍጡራን አለም ከሰሩበት
በከተማ መሐል ገነት የሚመስል አነስተኛ ገነት ከቆረቆሩበት
አዎን እዛ ሰፈር አንድ ሁለት ብዬልሽ
ባየሁት ያልሽውን ስካር ሰክሬልሽ
ቆምያለው ብቻዬን አንቺን እያሰብኩኝ
ለሊቱ ተጋምሷል ለኔ ግን ነጋልኝ
ሰሞኑን አንቺዬ ያመጣሁት ፀባይ
ለሰው ሲጨልም ነው እኔ ንጋት የማይ
ብቻ ቆሜ ሳለው ድንጋዩን አየሁት የጎዳናውን ጠርዝ
ባሳቤ ውስጥ አየው የፍቅርን ስንደዶ ከሰፌዱ ስንመዝ
ቱ.. አፌን እሳት ይፍጀው
ታቦት ፅላቴን ነው ድንጋይ ነው የምለው?
ያ ድንጋይ ለኔማ ከአክሱም በላይ ነው
ፍቅርሽ እና ፍቅሬ በፍቅር የጠረበው
ያ ድንጋይ ለኔማ የምስጢር ፅላት ነው
በስውር መዳፋ ስውር ድብቅ ህመም እግዜር የቀረፀው
ሙሴው የኔ መዳፍ ናፍቆት ሊሰባብር ለሁለት የከፈለው
እናም ይሄ ፅላት የጎዳናው ማዕዘን
ከንፈር አነካክሶ ዙፋን ሲሸልመን
በንግስና ዳና የረገጥነው ወጉ
ያ ነው ለኔ ማለት የ1 እርምጃ ጥጉ
...
የሰካራም ነገር ምን አስቀባጠረኝ
ብቻ ምን አለፋሽ ከዚሁ ድንጋይ ስር እርምጃ ጀመርኩኝ
.....
ከቦሌ እስከ ማርያም አራት እርምጃ ነው
ናፍቆትሽ ሲመራኝ እኔ ምራመደው
ፅላቴን አልፌ አይኔን ስወረውር
ልቤ ተላተመ ከአንድ ደጅ እግር ስር
እግዜር ይቀድሰው የደጃፉን ሰሪ ያፀዱን ባለቤት
ከበራፉ አብቧል የፍቅራችን ትንፋሽ የፍቅራችን ሂወት
ለኔና ለልቤ ላንቺና ለልብሽ ከለላ ለመሆን ጥላውን የጣለው
እሳት ከከለለው ከገነት ደጅ ይልቅ ይሄ ደጅ ንዑድ ነው
እርምጃ ቁጠሪ ከደጁ ትይዩ እስከ ማርያም ድረስ
ሁለት ይቀረናል ፍቅርሽን ለመሸሽ ፍቅሬ ጋ ለመድረስ
----------------------------

ከቦሌ እስከ ማርያም አራት እርምጃ ነው
ስሰክር ስሰክር ወይ ሲለኝ ድንግር ግር
እኔ የምራመደው።
እህ በይኝ እና ልንገርሽ አንቺዬ ስሚኝ ባዛኝቱ
ባይጥምም አይመርም ያፍቃሪ እውነቱ
የናፍቆት ዝለቱ
እህ በይ እህ በይ እህ በይ በማርያም ሰሚው እውነታዬን
ስሰክር ስከፋ የምረግጠውን ሃቅ የውነት እርምጃዬን
ሶስተኛው እርምጃ ከሁሉም ይልቃል
እዚኛው ገፅ ላይ ልቤ ምት ያቆማል
ምክኒያቱም አለሜ
ይሄ ሰፈርሽ ነው የግዛትሽ ጥለት
በሌት አነደደኝ የፀሐይሽ ግለት
ሰማይ በዚ ቦታ ሁሌም የጠራ ነው
ጨለማውን ሊገልጥ ኮከብ ጨረቃ ነው
360 ቀን ፀሐይ አትዞርም
ለ30 ቀናት ጨረቃም አትጎልም
እንደ ፀባኦቱ ልክ እንደ ማደርያው
የመቅደስ እጣን ነው የዚ ሰፈር ሽታው
ለካንስ በሌሊት እንደኔ ሲሰክሩ
እዚ ሰፈር አለ የመለኮት ክብሩ
ብቻ ምን አለፋሽ
የዳዊት በገና የእዝራ መሰንቆ
እዚ ሰፈር አለ ቤትሽ ተደብቆ
በቦዘዘው አይኔ እጣኑን ብጠራ እግዚያርን ባየው
አልጠየቅ እኔ ይሄ ሰፈርሽ ነው
የማይጠፋው ፋኖስ የማያልቀው ሻማ
በርምጃዬ መሐል አለ ፍቅርሽ ' እማ '
ሰሶስተኛው እርምጃ እንደተረገጠ ነጋ መሰል ሌቱ
ድሮስ ከሰፈርሽ አይደለም አለሜ የዚ ንጋት ቤቱ?
-----------------------------
ከቦሌ እስከ ማርያም አራት እርምጃ ነው
አይንሽን ስራበው
ክንድሽን ስራበው
ልብሽን ስራበው
እኔ የምራመደው።
አራተኛው ዱካ የልቤ ማረፍያ
የእመቤቴ አፀድ የልፍኟ መኖርያ
ድሮም የፍቅር ገፅ ሲነበብ አርስቱ
ልብ ነው የሚደርስ ከገፁ ፍፃሜ ከማርያም ከእናቱ
ከቦሌ እስከ ማርያም አራት እርምጃ ነው
ልቤ ደጇን ሲራብ እናት ሲናፍቀው
እግሬ የሚራመደው
አናጭ አፍራሽ ልጅሽ የመንገዱ ጌታ የርምጃ ፈጣሪ
ቅድስት የተባረክሽ አስታርቀሽ አዳሪ
ታድያ ከደጃፍሽ ጋን የሚያስንቅ ልሳት የረከሰ ገላ
ይዤ ምቆምበት አላገኝም ጥላ
ይልቅ ተሻግሬ ከመንገዱ ማዶ
እኔ ልጅሽ አለኝ
የምነግርሽ ብስራት የማረዳሽ መርዶ
- ብስራት
የምስራች ማርያም
የማፈቅራት ፍቅሬ ያቺ ውብ አበባ
ልትሞሸርልሽ ከደጃፍሽ ቀርባ
ቀናቱን ቆርጣለች
እናቴ ጠብቂያት ተክሊል አዘጋጅተሽ
- መርዶ
ከሰፈሬ ደጅሽ እስክመጣ ድረስ የረገጥኩት መንገድ
ያደከመኝ እግሬ ስካሬም እስኪበርድ
ከዚው ከደጃፍሽ እንዳታስጠልይኝ
እማምላክ እናቴ ፍቃድሽን ስጪኝ
ስለ እማምላክ ብዬ ልብ እያራራውኝ
ጉርሴን እንድበላ ስምሽን አውሽኝ
በንተ ስምሽ ልኑር እስኪለቀኝ ስካር
ፈቅደሽ ካደረግሽኝ ያድባርሽ ስር አድባር
ልመና ነበረኝ ስለ ቸርነትሽ
ለኔ ተለመኝኝ እማምላክ እባክሽ
አበርችኝ እናቴ ልቤ እንዳይዝልብኝ
ሰርጓን ባላደምቅም እንቅፋት እንዳሎን ቀናት ለምኝልኝ።

ተፈፀመ።
ALONE : @termo_dynamics

©ቅንጭብጭብ ኢትዮጵያ
Forwarded from @እንደኔ እይታ..... (Daree)
#ማስጠንቀቂያ

#የአይን_ብሌናችንን_እንዳናጣ_ጥንቃቄ

የሰኔ 14/2012 ዓ.ም የፀሐይ ግርዶሽን በተመለከተ የቀረበ መረጃ፡፡

🌑የ2012 ዓ.ም ግርዶሽ የሚታየው፡-

- ሰኔ እሁድ 14/2012 ዓ.ም ነው፣
- በግርዶሹ 6፡00 ሰዓት የሚፈጅ ጨለማ ይታያል፡፡
- በመላ ኢትዮጵያ ይታያል፡፡
- በተለይ ወለጋ፣ ጎጃም፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ አላማጣ፣ ኢንጂባራ 98% ጨለማ ሆኖ ይታያል፡፡
- የዓለምን አሰራር የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካን፣ የከፍተኛ የተፈጥሮ ኃይል ሊገኝ ይችላል ብለው ሳንቲስቶች ሀሳባቸውን እየሰነዘሩ ይገኛሉ፡፡

- ከምዕራብ ኢትዮጵያ እስከ ሰሜን ኢትዮጵያ ድረስ ግርዶሹ ይታያል፡፡
- ፀሐይ 98% ትሸፈናለች፡፡

🌑የሚታይበት እና የሚያበቃበት፡-

- ከማዕከላዊ አፍሪካ ከኮንጎ ይነሳል፣ ሱዳን፣ ኢትዮጵያ፣ የመን፣ ፓኪስታን፣ ታይዋን፣ ንድና ቻይናን አቋርጦ ፓስፊክ ውቂያኖስ ላይ ያበቃል፡፡


🌑ሙሉ ግርዶሹ የሚታይበት ወቅት

- ከሌሊቱ ሰኔ 14/2012 ዓ.መ
- 11፡00 ሰዓት ይጀምራል፣
- ከጠዋቱ 12፡45 እስከ ቀኑ 6፡33


‼️ማስጠንቀቂያ፡-

- በዓይን ለማየት አይቻልም ዐይን ያሳውራል፣
- በሱቅ ውስጥ የሚሸጥ መነጽር መጠቀም አይገባም፡፡
- ለፀሐይ ግርዶሽ ተብሎ የተዘጋጀ መነጽር አለ፡፡
- መነጽሩ አገር ውሰጥ አይገኝም፡፡
-ለፀሀይ ግርዶሽ የሚሆን መነፀር አለን ከሚሉ አጭበርባሪዎች ጥንቃቄ ያድርጉ
- ሲጨልም ማየት እንችላለን ነገር ግን ያለመነጽር ለማየት አንሞክር፣በጣም ጥንቃቄ ሊታከልበት ይገባል
- ዐይናችን ሊፈስ ይችላል፣


አብዛኛው ኢትዮጽያዊ መረጃው ስሌለው እና የፀሀይ ግርዶሽ የሚታይበት ቀን ስለደረሰ ቢያንስ ለ ሚወዷቸው 50 ሰወች ሼር በማድረግ መረጃው ለሁሉም እንዲደርስ በማድረግ ከህሊና ፀፀት ድነው የበኩልውን ይወጡ

🎖ዶ/ር ሊያ ታደሰ

@endenaendena
@endenaendena
…………………………
……………………………

"..........ግጥም ላንብብላችሁ አለ ?! " ባለቅኔው ሙሉጌታ ተፈቀደለት ።

ግጥሞቹ በየሰው እጅ ነው የሚገኙት ከጻፈ በኋላ የትም ይጥለዋል ። ለነገሩ የግጥም ሐሣብ ሲመጣለት ዛር እንዳለበት ያደርገዋል …… ያጣድፈዋል ።

" አስዬ ጨብራሪት መጣች ፣ አስዬ ጨብራሪት መጣች ፣ አስዬ ጨብራሪት መጣችብኝ … " ብሎ ይቁነጠነጣል ።

አስዬ ጨብራሪት የምታስፅፈው ዛር ናት ። ይህች ዛር ከመጣች አሁኑኑ ነው የምታስብለው ። በዚህ ጊዜ አጠገቡ ካሉ ሰዎች መካከል (ለምሣሌ ስንዱ) እስኪርብቶ አንስታ የሚለውን ትገለብጣለች ። አምስት …… ስድስት ወይም ሰባት ገጽ ሊሆን ይችላል። " በቃሉ ነው የሚያወጣቸው " ሲባል ሰምቻለው ያልተጻፉ ግጥሞቹን ። ከተጻፈ በኋላ አይሰርዝም አይደልዝም ።

ከዛ " አንብቢልኝ " ይላል ። ታነብባለች " ሸላይ ናት " ይላል በቃ ። ከእነዚህ ግጥሞች አንዱን አንብቦልን ሲጨርስ አስተያየት ጠየቀን ። እኔም የሚደነቀውን አድንቄ " .....ግን ከመጠን በላይ ረዥም ነው " አልኩት ። ፈጣን መልስ ሰጠኝ ።

" አንተ የበልግ ካፊያ ከሆንክ እኔ የሐምሌ ወጀብ እንዳልሆን ልትከለክለኝ አይገባም " አለኝ።

ቀደም ሲል አጫጭር ግጥሞች አቅርቤ ስለነበር ነው ። ግጥሞቼ በበልግ ካፊያ የመሰላቸው ።

" ጋሽ ስብሐት እንዴት አየሃት? " ጠየቀ።

" አልሰማኋትም ...... " አለው ስብሐት ።

" አትኩረህ እያየኸኝ አልነበር ? "

" ..........መጀመሪያ ልሰማህ ጓጉቼ ነበር ። ቆይቶ ግን የግጥሙ ርዝመት ይሁን የቋንቋው ክብደት አላውቅም እኔና አንተን ለመለያየት ምክንያት ሆነን ። እናም አየሰማሁህ ጺምህን ሳይ ፣ ፊትህን ሳይ በስዕል የማውቀው የራሺያው ዶስቶቪስኪን መሰልከኝ ። አዬ መመሳሰል ብዬ ስገረም ስገረም ግጥምህን ጨረስከው አንድ ቀን ትደግምልኛለህ! " አለው።

{እንዳለጌታ ከበደ ፤ ከማዕቀብ መጽሐፍ የተቀነጨበ ።}


╭══•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀: ══╮
ውብ አሁን
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ ══╯


┄┄┉✽̶»̶̥ ͜͡ ❀🌼❀ ͜͡»̶̥✽̶┉┄


┄┄┉✽̶»̶̥ ͜͡ ❀🌼❀ ͜͡»̶̥✽̶┉┄
The account of the user that owns this channel has been inactive for the last 11 months. If it remains inactive in the next 27 days, that account will self-destruct and this channel will no longer have an owner.
The account of the user that owns this channel has been inactive for the last 11 months. If it remains inactive in the next 20 days, that account will self-destruct and this channel will no longer have an owner.
The account of the user that owns this channel has been inactive for the last 11 months. If it remains inactive in the next 7 days, that account will self-destruct and this channel will no longer have an owner.
#ሀንግ #ኦቨር

የደሀውን ለቅሶ ~ የምስኪኑን ጩኸት
አላሰማም ብሎህ ~ የቢላዎች ፉጨት
ነብስህ ተከልላ ~ በስጋ አለም ስላቅ
ከታናሽ ላይ ቆርጠህ ~ አጉርሰህ ለታላቅ
ለማወራረጃ ~ ብርጭቆ ብትይዝም
ቀዝቀዝ ያለ ሁሉ ~ አያቀዘቅዝም
አያጠፋልህም
የነብስህን እሳት ~ ከስጋህ ነጥሎ
አያበርድልህም
የውጪው ቀዝቃዛ ~ የውስጥን ቃጠሎ
እውነቱ እንደዚህ ነው ~ እመነኝ ግዴለም
ከእርዛት ነጥቆ ~ በሚደርብ አለም
የሚያልበው ሁሉ ~ የሞቀው አይደለም

#ዛሬ
በንብረትህ ብዛት~ፍቃድ ስር ብትወድቅም
በጉብዝናህ ወራት ~ ለማሰብ ባትፈቅድም
ልክን ማሳወቅ ነው ~ የመለኪያ ጥቅም

#ከሰማህ #ልንገርህ
ግፍ እንደ ፍግ ሆኖህ
ከእድሜህ በላይ በቅለህ~ከሀገሬው ብትበልጥም
ደሀ ባፈሰሰው
የእንባ በረዶ ~ ውስኪ አይጨለጥም
===||===
ከሙሉቀን ሰ•