AddisWalta - AW
45.4K subscribers
42K photos
205 videos
20 files
16.7K links
This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.

For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured
Download Telegram
#አዳማ
#ከተሞቻችን

"የስምጥ ሸለቆ እንቁ" ተብላ የምትሞካሸው የአዳማ ከተማ ከመዲናችን አዲስ አበባ 99 ኪ.ሜ ላይ ትገኛለች፡፡

"አዳማ" የሚለውን ስያሜዋን ያገኘችው "አዳሚ" ከሚለው የአፋን ኦሮሞ ቃል ሲሆን ትርጓሜውም "ቁልቋል" ወይም "የቁልቋል ዛፍ" ማለት ነው፡፡

1 ሺሕ 712 ሜትር ከባህር ጠለል ከፍታ ላይ የምትገኘው ይህች ከተማ ቆላማ የአየር ንብረት ሲኖራት በአብዛኛው ሜዳማ የመሬት አቀማመጥ እና አሸዋማ የአፈር ተፈጥሮ አላት።

የከተማዋ መገለጫ የሆነው "የኦሮሞ ሰማዕታት ሀውልት" ከአባገዳ አዳራሽ ፊትለፊት የሚገኝ ሲሆን ይህም በከተማው መግቢያ ላይ የሚገኝ ነው።

ከተማዋ የንግድ፣ የኢንዱስትሪ፣ የስብሰባ እና የመዝናኛ መዳረሻ በመሆኗ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ያለማቋረጥ የሚታይባትም ናት፡፡

የአዳማ ከተማ የመቻቻል፣ የአብሮነት እና በእንግዳ ተቀባይነት ተምሳሌት ተደርጋም ትወሰዳለች።

ለከተማዋ ምስረታ እና መስፋፋት ምክንያት ተደርጎ የሚነሳው የአዲስ አበባ - ጅቡቲ የባቡር መስመር ዝርጋታ ሲሆን ቀደምት ከሆነው የከሰል ባቡር ጀምሮ እስከአሁኑ የኤሌክትሪክ ባቡር ድረስ አንዱ የትራንስፖርቱ መዳረሻ ከተማ ሆናም ታገለግላለች።

በአዳማ ከተማ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገኙ ሲሆን አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ዩኒቲ ዩኒቨርስቲ እና ሪፍትቫሊ ዩኒቨርሲቲዎች ይጠቀሳሉ፡፡

የአዳማ ኢንዱስትሪ ፖርክ፣ አዳማ ቆርቆሮ ፋብሪካ እና አዳማ ትራክተር መገጣጠሚያን ጨምሮ የጨርቃጨርቅ እና አውቶሞቲቨ ፋብሪካዎችም በከተማዋ ይገኛሉ።

https://shorturl.at/djs09

በአዲስዓለም ግደይ