ውሉደ ብርሀን ሰ/ት/ቤ/ት🙏(ጫንጮ)
766 subscribers
84 photos
4 files
98 links
ሰንበት ትምህርት ቤት የመልካም ወጣት የመልካም ትውልድ መፍለቂያ ናት! ትውልድን ለበጎ ነገር የምታበቃ ናት፡፡


የጫንጮ ከተማ ደ/ብ/ቅ/እግዚአብሔር አብ እና ደ/ሲ/ቅ/ ኪዳነ ምህረት ቤ/ክ ው/ብ/ሰ/ት/ቤት ቻናል
ለሀሳብ እና አስታየት @weldebirhanbot @ty1921 ይጠቀሙ

ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ መልካም ነው፡፡
Download Telegram
ቅዱሳን መጽሐፍት ምን ይላሉ?:
🌾‹‹ኑ እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር›› (ኢሳ. ፩፥፲፰)🌾

መምህር ጳውሎስ መልክዐሥለሴ

በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ተጎሳቁለው ለእግዚአብሔር ባልተመቻቸ ስፍራ በመቆማቸው ምክንያት የደረሰባቸውን በደል መቋቋም ላቃታቸው እስራኤላውያን ከኃጢአት የሚያነጻው፥ የሚያጠራው እና ከሰይጣን ባርነት ነጻ የሚያወጣው እግዚአብሔር እንደሆነ ነቢዩ ኢሳያስ ነገራቸው፡፡ ለደረሰባቸው የጸጋ መገፈፍ እና የሕይወት መጎስቆል ሁሉ መፍትሔያቸው እግዚአብሔር መሆኑንም አሳወቃቸው፡፡  (ኢሳ. ፩፥፲፰)

ብዙ ጊዜ በሕይወት በሚገጥመን ፈተናና ችግር ምክንያት ራሳችንን በመመርመር እግዚአብሔርን መማጸንን የመሰለ መፍትሔ ወይም የድኅነት መንገድ የለም፡፡ እስራኤል ከእግዚአብሔር ርቀው፤ ወደ ቃሉ መጠጋት በአቃታቸው ጊዜ ነቢዩ ኢሳይያስ  የመጣባቸው መቅሠፍት የኃጢአታቸው ውጤት ስለነበረ እግዚአብሔር አጥቦ ቅዱሳን ልጆቹ ሊያደርጋቸው የተዘጋጀ አባት በመሆኑ ‹‹ኑ እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር›› አላቸው፡፡ (ኢሳ. ፩፥፲፰)

የሰው ልጅ በሕይወት ጎዳና ውስጥ ከፍተኛ የኃጢአት አዘቅት እና ተስፋ መቁረጥ ውስጥ የሚወድቀው  እግዚአብሔር ቸር መሆኑን ሳይረዳ ሲቀር ብቻ ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ቸርነት የተረዳ ሰው ኃጢአት ቢሠራ እንኳን እርሱ መሓሪ መሆኑን አውቆ ለንስሓ ወደ ፈጣሪው ይጠጋል፡፡ እስራኤል ግን ይህን ስላልተረዱ ሸሹ፤ እነርሱንም ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ አላቸው፤ ‹‹ኑ እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደአለላ ብትሆን እንደአመዳይ ትጸዳለች፤ እንደደምም ብትቀላ እንደባዘቶ ትጠራለች፤›› በደጅ ለሚንከራተቱት እና ጎዳና በመከራ ለሚንከላወሱት አባት ሊሆናቸው እነርሱም ልጆች ይሆኑት ዘንድ እግዚአብሔር እንደጠራቸው አሳወቃቸው፤ እግዚአብሔር ያነጻው እና ያጠበው ብቻ ይነጻልና፡፡ (ኢሳ. ፩፥፲፰)

የሰው ልጅ ለመንፈሳዊ ንጽሕና በእግዚአብሔር ሊታጠብ ያስፈልጋል፤  እግዚአብሔር ካላጠበው ሰው ሕይወት የለውም፡፡ በዮሐንስ ወንጌል እንደተጻፈው ጌታ በሐዲስ ኪዳን የደቀ መዛሙርቱን እግር ሲያጥብ ቅዱስ ጴጥሮስ ግን ስለ ትሕትናው ‹‹ጌታ ሆይ አንተ የእኔን እግር ታጥባለህን?›› አለው፤ ጌታ ግን መልሶ ካላጠብህሁ፥ ከእኔ ጋር ዕድል የለህም›› ብሎ መለሰለት፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹ጌታ ሆይ፥ እጄንና ራሴን ደግሞ እንጂ እግሬን ብቻ አይደለም፤›› አለው፡፡ (ዮሐ. ፲፫፥፮-፱)

ቅዱስ ዳዊት በኃጢአት ጎስቁሎና አድፎ ‹‹በሂሶጵ እርጨኝ፥ እነጻማለሁ፤ እጠበኝ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ›› ብሎ እንደጸለየው በኃጢአት ያደፍን ወገኖች ሁሉ እግዚአብሔር እንዲያጠራን ራሳችንን ያለመፍራት ወደ እርሱ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡ እስራኤል ከእነ እድፋቸው ሲመላለሱ ኃጢአት አለብኝ ብለው መሸሽ ትክክል እንዳልሆነ፤ እግዚአብሔርም ከኃጢአት እንዲያነጻቸው ይቀርቡት ዘንድ አስተማራቸው፡፡ ሰዎች በኃጢአታቸው ተጸጽተው ከተመለሱ ወደ አምላካቸው መቅረብ እንጂ መሸሽ የለባቸው፡፡ እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ የምድርን በረከት ትበላችሁ ብሏቸዋል፡፡ (መዝ. ፶፥፯፤ኢሳ. ፩፥፲፱)

የሰው ልጅ የመንፈሳዊ ሕይወት ስኬት ለእግዚአብሔር፣ ለሕጉም ከመታዘዝ  ይጀምራል፡፡ እሺ ማለት፣ መታዘዝ እና ራስን ለእግዚአብሔር አሳልፎ መስጠት ያስፈልጋል፡፡ እግዚአብሔር በግዴታ ሳይሆን በፈቃደኝነት የሚገዛን ቸር አምላክ ነው፤ የፍቅር አባት በመሆኑ እርሱ ሲገዛን ጥሩ ልጆች እንሆናለን፤ እግዚብአሔር ሲመራን በእውነት መንገድ እንጓዛለን፡፡ እራሳችንን ለእርሱም የምናስገዛው እግዚአብሔርን ስናውቀው ነው፤ ክርስቲያኖች ፈጣሪያችንን ማወቅ አለብን፡፡ ክርስትናም ማመን፣ መታዘዝ፣ መገዛትና መጽደቅ፣ ለሰማያዊ ርስት፣ ለማያልፍ፣ ለማያልቅ፣ ለማያረጅ እና ለልጅነት በረከት መዘጋጀት ነው፡፡ ልባችን ለእግዚአብሔር የምናስገዛው ሁለንተናችን በፍቅር ሲነካ ነው፡፡ እግዚአብሔር ከሕይወት ጽልመት፣ ከኑሮ ጭጋግ እና ከሰብእና ውድቀት ሊጠብቀን ሲሻ ‹‹ልጄ ሆይ÷ ልብህን ስጠኝ÷ ዓይኖችህም መንገዴን ይውደዱ፤›› አለን፡፡ ልብ የሰውነታችን መሪ፤ ከአካል ክፍላችን ሁሉ በላይ ነውና፡፡ ሰው ዓይኑ ቢጠፋ በሕይወቱ ይኖራል፤ የልባችን መሥራት ካቆመ ግን ይሞታል፡፡  (ምሳ. ፳፫፥፳፮)

‹‹ልባችሁን ስጡኝ›› እንጂ ዓይናችሁን፣ እጃችሁን፣ እግራችሁን ወይንም ሌላ አካላችሁን ስጡኝ›› አላለም፡፡ ዋናውን አካላችንን እንድንሰጠው እና እርሱ ኃይል እንደሚሆነን ነገረን፤ እስራኤላውያን በተመሰቃቀለ መንገድ ላይ በመሆናቸው ሳቢያ በመቅሠፍት መመታታቸው ልባቸውን ስላልሰጡት እንደሆነ ነገራቸው፡፡ በችግር መደቆሳቸው፣ ጦርነት እና በሽታም ያጠቃቸው ልባቸውን ለእርሱ ባለመስጠታቸው መሆኑን አስረዳቸው፡፡

ዛሬም ሀገር በሰላም የምትተዳደረው ሰዎች ልባቸውን ለእግዚአብሔር ሲሰጡ ነው፡፡ ከትንሽ እስከ ትልቅ፤ ከልሒቅ እስከ ደቂቅ ያለው ሰው ሁለንተናውን ሊሰጥ ይገባል፤ የሰው ልጅ ሕይወቱን ለፈጣሪው ሲሰጥ ድኅነትን ያገኛል፤ ይባረካልም፡፡ ካላንበት የኑሮ አዘቅት ውስጥ ስቦ የሚያወጣን እግዚአብሔር ልባችንን ስንሰጠው እንደሆነ ነግሮናል፡፡ ፈጣሪያችን ሲመራን አንሰናከልም፤ አንሰበርም፤ አንታመምም፡፡  በእርሱ ዘንድ የማይጨልምበት ጌታ በድቅድቅ ጨለማ ወስጥ ብርሃን ይሆነናል፤ እግዚአብሔርን የምትወድ ነፍስ በብርሃን ትጓዛለች፡፡ ‹‹እግዚአብሔርም ሁል ጊዜ ከአንተ ጋር ይኖራል፤ እንደ ነፍስህም ፍላጎት ያጠግብሃል፤ አጥንትህንም ያለመልማል፡፡ አንተም እንደሚጠጣ ገነት÷ ውኃውም እንደማያቋርጥ ምንጭ ትሆናለህ›› እንዲል፡፡ (ኢሳ. ፶፰፥፲፩)

እግዚአብሔር የሚመራን ከሆነ ሀገር በበረከት ሕዝብ በታዛዥነት ይጓዛል፤ ከመሪ ጀምሮ እስከ ተመሪ ለፈጣሪ መገዛት ያስፈልጋል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን በቤታችን ሀብት ብናገኝም ጤና እናጣለን፤ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የለምና፤ በሰላም ውለን የምናድረው እርሱ ሲፈቅድ ነው፡፡ ካልሆነ ግን ሀብቱ ቅዠት፤ ዕውቀቱ እብደት፤ ንግዳችን ኪሳራ ይሆናል፡፡

እግዚአብሔር የለም ብለው የሚያምኑ ሰዎችንም እንደ ምሁር መቁጠር ጀምረናል፤ ‹‹እርሱ እኮ ወጣ ያለነው እንላለን፤›› በእርግጥ የወጣ ነው፤ ከሕይወት ጎዳና የወጣ፣ ወደ ሞት ቁልቁለት የወረደ ማለት ነው፡፡ የክሕደት መርዛቸውን እየረጩ ብዙ ተማሪዎችን ሳይጨርሱ እንዲወድቁ ያደረጉ መምህራን አሉ፡፡ ዕውቀትና እድገት ይገኝበታል የተባሉ ትምህርት ቤቶች ዛሬ የዝሙት፣ የሴሰኝነት እና የርኩሰት መናኀሪያዎች ሆነዋል፡፡ ክፋት የሌለባቸውን ሕፃናት ከአቅማቸው በላይ ለሆነ ሐሳብ እየዳረግናቸው እንገኛለን፡፡

ከሕፃንነት ጀምሮ የመራንን አባት በእምነት እንከተለው፤ ጌታ ሆይ ከአማልክት መካከል እንዳንተ ያለ ማነው፤ አንተ ፈጠርከን፤ ስለወደድከን አሳደከን፤ ልጅህ አድርገህ አከበርከን፤ በመንፈስ ቅዱስ የምትመራን አንተ ነህ፤ ኑሮአችን፣ ሥራአችን፣ ትዳራችን በአንተ ይሁን፤ እንቅስቃሴያችን፣ ንግግራችን፣ ልባችንና ሁለንተናዊ ማንነታችን ለአንተ ይሁን፤ አንተን የሚመስል የለም እንበለው፡፡

በማጣት፣ በማግኘት፣ በመራብም፣ በመጥገብም፣ በማትረፍም፣ በመክሰርም፣ በመሾምም፣ በመሻርም፣ ክርስቲያን ተመስገን ማለት አለበት፡፡ምድራዊ ሕይወታችን የምንማርበት እንጂ የምናማርርበት ሊሆን አይገባም፤ ‹‹እግዚአብሔር ሊያስተምረኝ ፈልጎ ነው›› ብለን ተመስገን ማለት አለብን፡፡
ክርስቲያን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከበደላችን ነጻ ሊያደርገን ሰው የሆነ፤ ለክብራችን የተዋረደ፤ ወድቆ ያነሳን፤ ታሞ የፈወሰን አባት እንደሆነም መዘንጋት የለበትም፡፡   በአኗኗራችን አንሰን፣ በበሽታ ተጎድተን፣ በሕይወት ጎስቁለን ብንኖርም ሕመማችንን የሚፈውስልን አባት እግዚአብሔር ‹‹ኑ›› ይለናልና ወደ እርሱ እንቅረብ፡፡

በመንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ እሺ ብሎ መታዘዝ ሰዎችን ለክብር ያበቃል፤ እንቢ ያልን ሰዎች ካለን ዛሬ እሺ በማለት ወደ እግዚአብሔር እንቅረብ፤ ዘወትር ለእኛ የሚያስብልን ጌታ፣ የማይተወን ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ይሁን፤ አሜን፡፡
https://t.me/yeberhanljoche
💥 እግዚአብሔር ድንቅ ሥም 💥

እግዚ-አብ-ሔር ማለት የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስን ስም የያዘ ቅዱስ ሥም ነው።

#እግዚ

አግአዘ - ነፃ አወጣ ነፃ ፍቃድ ሰጠ .. አግአዞ ለአዳም- አዳምን ከዲያቢሎስ ነፃ አወጣው

እግዚኦ - ጌታ ሆይ ነፃ አውጣን

ግእዝ - ነፃ መውጣት

እግዚእነ እግዚ-ኦ : እግዚ-አብ-ሔር:

እግዚ - አግአዚ ነፃ አውጪ አጋእዝት አጋዚያን "ጌታ /እግዚአብሔር አብ/ ጌታዬን / ኢየሱስ ክርስቶስን/ ጠላቶችህን ለእግርህ መቀመጫ እስካደርግልህ በቀኜ ተቀመጥ አለው። መዝ.109፥10 - " እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ።" (ዕብ 2:14-15)

ነጻ ያወጣን ኢየሱስ / ወልድ/ እግዚ ነው።


#አብ

አብ- አባ: አባት ዘላለማዊ አባት የሆነ እኛን ፈጥሮ ፈጣሪነቱን የገለፀና ቸርነቱን የአሣየን ነውና አባትነቱ ያለ የነበረ የሚኖር ዘላለማዊ ህይወት ሠጭ ነው "ሁላችን አንድ አባት የአለን አይደለምን? አንድ አምላክ የፈጠረን አይደለምን? " ሚል. 2፥10

#ሔር

ሔረ - ለገሰ:ሰጠ: ቸር ሆነ: ቅን ሆነ
ሔር -ቸር ለጋስ ደግ ቅን ሰጭ
ሒሩት- ቸርነት ደግነት ለጋሽነት ቅንንነት

ሔር-ቸር "ሃሌ ሉያ ቸር ነውና ምህረቱ ለዘለአለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑት" መዝ.105:1
"እግዚአብሔር ቸር እንደሆነ ቅመሱ እዩምበእርሱ የሚታመን ምስጉን ነው" መዝ.33፥8 " ከአንዱ እግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም" ማር.10፥18 ሉቃ. 18፥18

የእግዚአብሔር ፍቅሩ ይደርብን።

#ማጠቃለያ
እግዚ=ጌታ( ለወልድ)
አብ= አባት(ለአብ )
ሔር= ቸር (ለመንፈስ ቅዱስ )
@yeberhanljoche
@yeberhanljoche
@yeberhanljoche
ንቃ የተዋህዶ ልጅ አከባቢ ያለውን ቤተክርስቲይን ጠብቅ 😭😭😭😢😢😢
ስማኝ ልጄ!!!!!!!

1. ጠንካራ ሰው ሁን ማለት አትውደቅ ማለት አይደለም ወድቀህ መነሳትንም ልመድ ማለት እንጂ!!!!

2. ዝም በል ማለት አትናገር ማለት አይደለም ሌሎችን ለመስማት ጆሮ ስጥ ማለት እንጂ!!!!

3. ሆዳም አትሁን ማለት አትብላ ማለት አይደለም በሰው ሀቅ አትለፍ ማለት እንጂ!!!!

4. አትቆጣ ማለት ስሜት አይኑርህ ማለት አይደለም ከቁጣ ቶሎ ተመለስ ማለት እንጂ!!!!

5. ይቅርታ አድርግ ማለት አልተጎዳህም ማለት አይደለም በሆድህ ቂም መያዝ ሌላ ጉዳት ስለሆነ እንጂ!!!!

6. ጠላትህን ውደድ ማለት ጠላት ጥሩ ነው ማለት አይደለም ከጥላቻ ይልቅ ፍቅር ስለሚያሸንፍ!!!

7. ደስተኛ ሁን ማለት ሁሉ ይኑርህ ማለት አይደለም ባለህ ነገር ደስ ይበልህ ማለት እንጂ!!!!

8. ስራህን ውደድ ማለት የምትሰራው ስራ ጥሩ ነው ማለት አይደለም ነገ ጥሩ ስራ እንዲኖርህ ዛሬ የምትሰራውን ስራ ውደድ ማለት እንጂ!!!!

9. ወረኛ አትሁን ማለት አታውራ ማለት አይደለም ምንም ስለማታውቀው ነገር አታውራ ማለት እንጂ!!!!

10. ትሞታለህ ማለት አትስራ ማለት አይደለም ምንም ቁም ነገር ስትሰራ አትሙት ማለት እንጂ!!!!

11. ብቸኛ አትሁን ማለት ሮጠህ ትዳር ያዝ ማለት አይደለም ልብህን ግዜህን ያለህን ሁሉ አሳልፈ ለመስጠት ዝግጁ ሁን ማለት እንጂ!!!!

12. እውነተኛ ሁን ማለት ሰዎች ባሉበት ብቻ እውነትተናገር ማለት አይደለም ለራስህም የእውነት ኑሮ ኑር ማለት ማለት እንጂ!!!!

13. አትጣላ ማለት ከሰው ጋር አትኑር ማለት አይደለም ቂም ይዘህ አትቆይ ማለት እንጂ!!!!

14. ኩራተኛ አትሁን ማለት አትዘንጥ ማለት አይደለም ሌሎችን አትናቅ ማለት እንጂ!!!

15. ቆንጆ ነህ ማለት ከሌሎች የተሻልክህ ነህ ማለት አይደለም አምሮብሃል ማለት እንጂ!!!!

16. አዋቂ ሁን ማለት እንደገና ት/ቤት ሂድ ማለት አይደለም ብልህ ሁን ማለት እንጂ!!!!

@yeberhanljoche
@yeberhanljoche
@yeberhanljoche
Audio
​​✞ መከራው ክርስትናዬን አጣፈጠው ✞

መከራው ክርስትናዬን አጣፈጠው
ስደቱ ማህተቤን አጠበቀው
በሞት መንደር በሀዘን ውስጥ በመከራ
አየውት እግዚአብሔርን ከኔ ጋራ

ክርስትያን ተብለን በክርስቶስ ስም የተጠራነው
በጥልቁ ውስጥም በእግዚአብሔር እንድናምን ነው
ለጥቂት ግዜ ቢበረታብን ስደት ሀዘኑ
አምላክ ግን መውጫ ያዘጋጃል በዚህ ተፅናኑ

አዝ__

በስደት ለን ካፋችን ቢደርቅ የፅዮን ዜማ
ከወንዙ አጠገብ ቁጭ ብለን ሰለን ድምፁን ሳንሰማ
በእግዚአብሔር ጊዜ ከባቢሎን ምድር እንለቃለን
መሰንቆአችንን ከአርያም ዛፍ ላይ እናወርዳለን

አዝ__

ደካሞች ሲሉን በስሙ ያን ጊዜ እንረታለን
ድሆች ስንባል ባለጠጎች እናደርጋለን
በምድር ቅዱስ ህዝብ አድርጎ ለእርሱ ለየን
ጨለማው አልፎ በቸርነቱ ብርሀን አሳየን

አዝ__

ከፀጋ በላይ እንዳንፈተን ይከልለናል
በቁስላች ላይ የፈውስ ዘይት ያፈስልናል
በጊዜም ቢሆን ያለ ጊዜውም በእርሱ እንፅና
እንኳን ስደቱን ሞቱን ሊገታው ይችላልና

ሊቀ-መዘምራን
ዲያቆን ቴድሮስ
@webzema
Forwarded from Acorns
💵ስልኮን በመጠቀም በወር እስከ 10,000 ብር በላይ ተከፋይ ይሁኑ 😱

🔅የ Acorns ቦት ጋር ልክ እንደገቡ የ 100 ብር ስጦታ ያገኛሉ በተጨማሪም 1 ሰዉ ወደ ቦቱ ሲጋብዙ በየቀኑ የ 50 ብር ቋሚ ክፍያ


🔥ይህ የእርሶ የመጋበዣ link ነው ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ 👇👇
https://t.me/FreeEearnMoneyPay_Bot?start=r0475648302
ቅዱሳን መጽሐፍት ምን ይላሉ?:
🌾‹‹ኑ እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር›› (ኢሳ. ፩፥፲፰)🌾

መምህር ጳውሎስ መልክዐሥለሴ

በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ተጎሳቁለው ለእግዚአብሔር ባልተመቻቸ ስፍራ በመቆማቸው ምክንያት የደረሰባቸውን በደል መቋቋም ላቃታቸው እስራኤላውያን ከኃጢአት የሚያነጻው፥ የሚያጠራው እና ከሰይጣን ባርነት ነጻ የሚያወጣው እግዚአብሔር እንደሆነ ነቢዩ ኢሳያስ ነገራቸው፡፡ ለደረሰባቸው የጸጋ መገፈፍ እና የሕይወት መጎስቆል ሁሉ መፍትሔያቸው እግዚአብሔር መሆኑንም አሳወቃቸው፡፡  (ኢሳ. ፩፥፲፰)

ብዙ ጊዜ በሕይወት በሚገጥመን ፈተናና ችግር ምክንያት ራሳችንን በመመርመር እግዚአብሔርን መማጸንን የመሰለ መፍትሔ ወይም የድኅነት መንገድ የለም፡፡ እስራኤል ከእግዚአብሔር ርቀው፤ ወደ ቃሉ መጠጋት በአቃታቸው ጊዜ ነቢዩ ኢሳይያስ  የመጣባቸው መቅሠፍት የኃጢአታቸው ውጤት ስለነበረ እግዚአብሔር አጥቦ ቅዱሳን ልጆቹ ሊያደርጋቸው የተዘጋጀ አባት በመሆኑ ‹‹ኑ እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር›› አላቸው፡፡ (ኢሳ. ፩፥፲፰)

የሰው ልጅ በሕይወት ጎዳና ውስጥ ከፍተኛ የኃጢአት አዘቅት እና ተስፋ መቁረጥ ውስጥ የሚወድቀው  እግዚአብሔር ቸር መሆኑን ሳይረዳ ሲቀር ብቻ ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ቸርነት የተረዳ ሰው ኃጢአት ቢሠራ እንኳን እርሱ መሓሪ መሆኑን አውቆ ለንስሓ ወደ ፈጣሪው ይጠጋል፡፡ እስራኤል ግን ይህን ስላልተረዱ ሸሹ፤ እነርሱንም ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ አላቸው፤ ‹‹ኑ እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደአለላ ብትሆን እንደአመዳይ ትጸዳለች፤ እንደደምም ብትቀላ እንደባዘቶ ትጠራለች፤›› በደጅ ለሚንከራተቱት እና ጎዳና በመከራ ለሚንከላወሱት አባት ሊሆናቸው እነርሱም ልጆች ይሆኑት ዘንድ እግዚአብሔር እንደጠራቸው አሳወቃቸው፤ እግዚአብሔር ያነጻው እና ያጠበው ብቻ ይነጻልና፡፡ (ኢሳ. ፩፥፲፰)

የሰው ልጅ ለመንፈሳዊ ንጽሕና በእግዚአብሔር ሊታጠብ ያስፈልጋል፤  እግዚአብሔር ካላጠበው ሰው ሕይወት የለውም፡፡ በዮሐንስ ወንጌል እንደተጻፈው ጌታ በሐዲስ ኪዳን የደቀ መዛሙርቱን እግር ሲያጥብ ቅዱስ ጴጥሮስ ግን ስለ ትሕትናው ‹‹ጌታ ሆይ አንተ የእኔን እግር ታጥባለህን?›› አለው፤ ጌታ ግን መልሶ ካላጠብህሁ፥ ከእኔ ጋር ዕድል የለህም›› ብሎ መለሰለት፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹ጌታ ሆይ፥ እጄንና ራሴን ደግሞ እንጂ እግሬን ብቻ አይደለም፤›› አለው፡፡ (ዮሐ. ፲፫፥፮-፱)

ቅዱስ ዳዊት በኃጢአት ጎስቁሎና አድፎ ‹‹በሂሶጵ እርጨኝ፥ እነጻማለሁ፤ እጠበኝ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ›› ብሎ እንደጸለየው በኃጢአት ያደፍን ወገኖች ሁሉ እግዚአብሔር እንዲያጠራን ራሳችንን ያለመፍራት ወደ እርሱ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡ እስራኤል ከእነ እድፋቸው ሲመላለሱ ኃጢአት አለብኝ ብለው መሸሽ ትክክል እንዳልሆነ፤ እግዚአብሔርም ከኃጢአት እንዲያነጻቸው ይቀርቡት ዘንድ አስተማራቸው፡፡ ሰዎች በኃጢአታቸው ተጸጽተው ከተመለሱ ወደ አምላካቸው መቅረብ እንጂ መሸሽ የለባቸው፡፡ እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ የምድርን በረከት ትበላችሁ ብሏቸዋል፡፡ (መዝ. ፶፥፯፤ኢሳ. ፩፥፲፱)

የሰው ልጅ የመንፈሳዊ ሕይወት ስኬት ለእግዚአብሔር፣ ለሕጉም ከመታዘዝ  ይጀምራል፡፡ እሺ ማለት፣ መታዘዝ እና ራስን ለእግዚአብሔር አሳልፎ መስጠት ያስፈልጋል፡፡ እግዚአብሔር በግዴታ ሳይሆን በፈቃደኝነት የሚገዛን ቸር አምላክ ነው፤ የፍቅር አባት በመሆኑ እርሱ ሲገዛን ጥሩ ልጆች እንሆናለን፤ እግዚብአሔር ሲመራን በእውነት መንገድ እንጓዛለን፡፡ እራሳችንን ለእርሱም የምናስገዛው እግዚአብሔርን ስናውቀው ነው፤ ክርስቲያኖች ፈጣሪያችንን ማወቅ አለብን፡፡ ክርስትናም ማመን፣ መታዘዝ፣ መገዛትና መጽደቅ፣ ለሰማያዊ ርስት፣ ለማያልፍ፣ ለማያልቅ፣ ለማያረጅ እና ለልጅነት በረከት መዘጋጀት ነው፡፡ ልባችን ለእግዚአብሔር የምናስገዛው ሁለንተናችን በፍቅር ሲነካ ነው፡፡ እግዚአብሔር ከሕይወት ጽልመት፣ ከኑሮ ጭጋግ እና ከሰብእና ውድቀት ሊጠብቀን ሲሻ ‹‹ልጄ ሆይ÷ ልብህን ስጠኝ÷ ዓይኖችህም መንገዴን ይውደዱ፤›› አለን፡፡ ልብ የሰውነታችን መሪ፤ ከአካል ክፍላችን ሁሉ በላይ ነውና፡፡ ሰው ዓይኑ ቢጠፋ በሕይወቱ ይኖራል፤ የልባችን መሥራት ካቆመ ግን ይሞታል፡፡  (ምሳ. ፳፫፥፳፮)

‹‹ልባችሁን ስጡኝ›› እንጂ ዓይናችሁን፣ እጃችሁን፣ እግራችሁን ወይንም ሌላ አካላችሁን ስጡኝ›› አላለም፡፡ ዋናውን አካላችንን እንድንሰጠው እና እርሱ ኃይል እንደሚሆነን ነገረን፤ እስራኤላውያን በተመሰቃቀለ መንገድ ላይ በመሆናቸው ሳቢያ በመቅሠፍት መመታታቸው ልባቸውን ስላልሰጡት እንደሆነ ነገራቸው፡፡ በችግር መደቆሳቸው፣ ጦርነት እና በሽታም ያጠቃቸው ልባቸውን ለእርሱ ባለመስጠታቸው መሆኑን አስረዳቸው፡፡

ዛሬም ሀገር በሰላም የምትተዳደረው ሰዎች ልባቸውን ለእግዚአብሔር ሲሰጡ ነው፡፡ ከትንሽ እስከ ትልቅ፤ ከልሒቅ እስከ ደቂቅ ያለው ሰው ሁለንተናውን ሊሰጥ ይገባል፤ የሰው ልጅ ሕይወቱን ለፈጣሪው ሲሰጥ ድኅነትን ያገኛል፤ ይባረካልም፡፡ ካላንበት የኑሮ አዘቅት ውስጥ ስቦ የሚያወጣን እግዚአብሔር ልባችንን ስንሰጠው እንደሆነ ነግሮናል፡፡ ፈጣሪያችን ሲመራን አንሰናከልም፤ አንሰበርም፤ አንታመምም፡፡  በእርሱ ዘንድ የማይጨልምበት ጌታ በድቅድቅ ጨለማ ወስጥ ብርሃን ይሆነናል፤ እግዚአብሔርን የምትወድ ነፍስ በብርሃን ትጓዛለች፡፡ ‹‹እግዚአብሔርም ሁል ጊዜ ከአንተ ጋር ይኖራል፤ እንደ ነፍስህም ፍላጎት ያጠግብሃል፤ አጥንትህንም ያለመልማል፡፡ አንተም እንደሚጠጣ ገነት÷ ውኃውም እንደማያቋርጥ ምንጭ ትሆናለህ›› እንዲል፡፡ (ኢሳ. ፶፰፥፲፩)

እግዚአብሔር የሚመራን ከሆነ ሀገር በበረከት ሕዝብ በታዛዥነት ይጓዛል፤ ከመሪ ጀምሮ እስከ ተመሪ ለፈጣሪ መገዛት ያስፈልጋል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን በቤታችን ሀብት ብናገኝም ጤና እናጣለን፤ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የለምና፤ በሰላም ውለን የምናድረው እርሱ ሲፈቅድ ነው፡፡ ካልሆነ ግን ሀብቱ ቅዠት፤ ዕውቀቱ እብደት፤ ንግዳችን ኪሳራ ይሆናል፡፡

እግዚአብሔር የለም ብለው የሚያምኑ ሰዎችንም እንደ ምሁር መቁጠር ጀምረናል፤ ‹‹እርሱ እኮ ወጣ ያለነው እንላለን፤›› በእርግጥ የወጣ ነው፤ ከሕይወት ጎዳና የወጣ፣ ወደ ሞት ቁልቁለት የወረደ ማለት ነው፡፡ የክሕደት መርዛቸውን እየረጩ ብዙ ተማሪዎችን ሳይጨርሱ እንዲወድቁ ያደረጉ መምህራን አሉ፡፡ ዕውቀትና እድገት ይገኝበታል የተባሉ ትምህርት ቤቶች ዛሬ የዝሙት፣ የሴሰኝነት እና የርኩሰት መናኀሪያዎች ሆነዋል፡፡ ክፋት የሌለባቸውን ሕፃናት ከአቅማቸው በላይ ለሆነ ሐሳብ እየዳረግናቸው እንገኛለን፡፡

ከሕፃንነት ጀምሮ የመራንን አባት በእምነት እንከተለው፤ ጌታ ሆይ ከአማልክት መካከል እንዳንተ ያለ ማነው፤ አንተ ፈጠርከን፤ ስለወደድከን አሳደከን፤ ልጅህ አድርገህ አከበርከን፤ በመንፈስ ቅዱስ የምትመራን አንተ ነህ፤ ኑሮአችን፣ ሥራአችን፣ ትዳራችን በአንተ ይሁን፤ እንቅስቃሴያችን፣ ንግግራችን፣ ልባችንና ሁለንተናዊ ማንነታችን ለአንተ ይሁን፤ አንተን የሚመስል የለም እንበለው፡፡

በማጣት፣ በማግኘት፣ በመራብም፣ በመጥገብም፣ በማትረፍም፣ በመክሰርም፣ በመሾምም፣ በመሻርም፣ ክርስቲያን ተመስገን ማለት አለበት፡፡ምድራዊ ሕይወታችን የምንማርበት እንጂ የምናማርርበት ሊሆን አይገባም፤ ‹‹እግዚአብሔር ሊያስተምረኝ ፈልጎ ነው›› ብለን ተመስገን ማለት አለብን፡፡
ክርስቲያን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከበደላችን ነጻ ሊያደርገን ሰው የሆነ፤ ለክብራችን የተዋረደ፤ ወድቆ ያነሳን፤ ታሞ የፈወሰን አባት እንደሆነም መዘንጋት የለበትም፡፡   በአኗኗራችን አንሰን፣ በበሽታ ተጎድተን፣ በሕይወት ጎስቁለን ብንኖርም ሕመማችንን የሚፈውስልን አባት እግዚአብሔር ‹‹ኑ›› ይለናልና ወደ እርሱ እንቅረብ፡፡

በመንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ እሺ ብሎ መታዘዝ ሰዎችን ለክብር ያበቃል፤ እንቢ ያልን ሰዎች ካለን ዛሬ እሺ በማለት ወደ እግዚአብሔር እንቅረብ፤ ዘወትር ለእኛ የሚያስብልን ጌታ፣ የማይተወን ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ይሁን፤ አሜን፡፡
https://t.me/yeberhanljoche
ቅዱሳን መጽሐፍት ምን ይላሉ?:
🌾‹‹ማእከለ አሥዋክ ዘጸገየት ጽጌ ሃይማኖት፤ በእሾሆች መካከል የበቀለች የሃይማኖት ተክል- ቤተ ክርስቲያን››🌾

(ቅዱስ ያሬድ)

በነቢያት ትንቢት በሐዋርያት ስብከት በክርስቶስ ደም የተመሠረተችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዘወትር ውድቀትና ጥፋቷን በሚሹ የውስጥና የውጭ ጠላቶቿ በዘመናት መካከል እጅግ በርካታ የሚባሉ ግፍና መከራዎችን አሳልፋለች፡፡እነዚህ ግፍና መከራዎችም ታሪክና ትውልድ የማይረሳቸው የዘመን ጠባሳዎቿ ሆነው አልፈዋል፡፡

አብያተ ክርስቲያናትን በአዋጅ አዘግተው አብያተ ጣዖታትን በአዋጅ ካስከፈቱት ከሐዲያን ነገሥታት ከእነ ዲዮቅልጥያኖስ መክስምያኖስ ዱድያኖስ ንግሥት አውዶክስያ እና ከሌሎቹ የግብር አበሮቻቸው ዘመን ጀምሮ ይህቺ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዘመናት መካከል ሕንፃዎቿ ሲፈራርሱ መምህራን ሊቃውንት ምእመናንና ካህናቶቿ በቤተ መቅደስ በሰይፍ ሲታረዱ በመጋዝ ሲሰነጠቁ በመንኰራኵር ሲፈጩ ወደ ጥልቅ ገደል ወደ እቶነ እሳትና ወደ አራዊት ጉድጓድ ሲወረወሩ እንደ ፈጣሪያቸው እንደ ክርስቶስ ሲሰቀሉ ቅዱሳት መጻሕፍቷና የከበሩ ንዋያተ ቅድሳቶቿ ሲዘረፉ ሲቃጠሉ ቅዱሳት ማካናቷ (ይዞታዎቿ) ሲነጠቁ እነዚህ ሁሉ መከራዎች በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ሲፈራረቁባት ኖረዋል፡፡

ይህ ሁሉ ሲሆን ግን ‹‹የገሃነም ደጆች ያነዋውጧት ዘንድ አይቻላቸውም›› ተብሎ እንደተጻፈ ይህቺ ቅድስት ቤተክርስቲያን በእነዚህ ሁሉ መከራዎች ውስጥ ብታልፍም ከፊት ከኋላዋ የሚገፋት የመከራ ማዕበል ሳያናውጻት ሃይማኖቱንና ባህሉን የሚጠብቅ ለነፃነቱ ለሀገሩና ዳር ድንበሩ ክብር የሚሠዋ ፈጣሪውን የሚያከብር ለመሪዎቹም የሚገዛ ግብረ ገባዊ ትውልድን በመቅረጽ ረገድ ጉልህ ድርሻን በማበርከት በሥነ ፊደል፣ በሥነ አኃዝ፣ በሥነ ሥዕል፣ በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብ፣ በኪነ ሕንፃና በሥርዓተ ሕግ ቀረጻ ሀገራዊ ክብርንና ዕሴቶችንም በማስጠበቅ በሀገር ግንባታ የሀገር ባለውለታነቷን በብቃት እያስመሰከረች እስከዚህኛው ዘመን ደርሳለች፡፡

በሚዳሰሱና በማይዳሰሱ ልዩ ልዩ መንፈሳዊና ቁሳዊ ቅርሶቿ የኢትዮጵያ መልካም ገጽታ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ፊት ጎልቶ እንዲወጣና ዕውቅናን እንዲያገኝ ያደረገች መንፈሳዊት ተቋም መሆኗን በግልጽ ያሳየቸው ታላቋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይህንን ታላቅነቷንም መሪዎች እንኳን ሳይቀሩ ‹‹ኦርቶዶክስ ሀገር ናት›› በማለት ኦርቶዶክስ ከተቋም በላይ ከፍ ብላ የምትታይ ታላቅ ሀገር መሆኗን በዐደባባይ በአንደበታቸው መስክረውላታል፡፡

ታዲያ ይህ ባለውለታነቷ በትውልድ ልቡና ውስጥ ተዘንግቶ ውለታዋ ወርቅ ላበደረ ጠጠር አለዚያም ባጎረስኩ እጄን ተነከስኩ ዓይነት ሆኖ ወርቅ የሰጠችው የመጨረሻው ዘመን ዓመፀኛ ትውልድ በላይዋ ላይ ጠጠርን እየደፋ ጥበብን ያጎረሰችበት እጅዋንም መልሶ እየነከሰ ዕለት ዕለት በመከራ ውስጥ እንዲታልፍ ያለፈውን የመከራ ዘመንም እንዲትደግም እያደረጋት ይገኛል፡፡ በዚህም ምክንያት የሚነድባትን እሳት ለማጥፋት የካህናትና ምእመናን ወገኖቿን ሕይወት ከሞት ለመታደግ በአጠቃላይ የሆነባትንና እየሆነባት ያለውን መከራዋን ሁሉ ለማስታገሥ ሀገርን ከሚመሩና በየደረጃው ከሚያስተዳድሩ የተለያዩ የመንግሥት ባለሥልጣናት የሀገር ሽማግሌዎች የሃይማኖት አባቶች የጎሣ መሪዎች ጋር ደግማ ደግጋማ መክራለች በልዩ ልዩ ሚዲያዎችም የሚፈጸምባትን ጥቃት መንግሥት እንዲያስቆም የምእመናን ልጆቿንም ሕይወት ከአጥፊዎች እንዲታደግ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጠቻቸው ጋዜጣዊ መግለጫዎች ደጋግማ ጠይቃለች፤ አሳስባለች፡፡

በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ አጥልቶ የሚታየው የጥቃት ድባብ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲማሩ ልጆቻቸውን የላኩ ወላጆችንም ሆነ ተማሪዎችን በተረጋጋ መንፈስ እንዲኖሩ የሚፈቅድ አይደለም። በአንዳንድ ቦታ አልፎ አልፎ እየተከሰቱ ያሉ አደጋዎችና ሁከቶች ወላጆችን ለከፍተኛ ሥጋትና ጭንቀት እየዳረጋቸው ነው፡፡

...

...

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመዋዕለ ስብከቱ በምድር ላይ እየተመላለሰ ወንጌልን ሲያስተምር በነበረበት ጊዜም ‹‹የሚወደኝ ቢኖር መስቀሌን ይሸከምና ይከተለኝ›› በማለት የሰዎችን ፈቃድ መሠረት አግርጎ ተከተሉኝ አለ እንጂ አምላክ በመሆኑ ክርስትናን አስገድዶ በማንም ላይ አልጫነም፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም የክርስቶስን ወንጌለ መንግሥት ለሰው ልጆች የምትሰብከው በደሙ የመሠረታትን የራሱን የክርስቶስን ትምህርት አብነት አድርጋ ነው፡፡

ይህ የግለሰቡ አነጋገር በዘር ፖለቲካና በጎጠኝነት አስተሳሰብ የተጠመዱ አካላት ብሔርንና ሃይማትን በአንድ ጨፍልቀው በመመልከት ቤተክርስቲያንን የአንድ ብሔር ወይም የአንድ አካባቢ ማኅበረሰብ የእምነት ተቋም፣ ኦርቶዶክሳዊት ክርስትናንም የአንድ ብሔር ሃይማኖት ሆና እንዲትታሰብ ለማድረግ ሲሆን ይህም በመንጋ በተደራጁ የጥፋት ኃይሎች ዘንድ አሁን ላይ በሚታየው ቤተክርስቲያንን፣ ክርስትናንን ክርስቲያኖችን የማጥፋት ዘመቻ የመጀመሪያዋ የጥቃት ዒላማና ሰለባ እንዲትሆን አድግርጓታል፡፡

ሚዲያው የራሳቸው ስለሆነ ብቻ የሕዝቦችን ነፃነትና ክብርን የሚገፋ የሀገርን ደኅንነትም የሚያናጉና በክፉ አስተሳሰባቸው ሌሎችን የሚያከፉ በንግግራቸው ከማስተማር ይልቅ ማሳመጽን ከፍቅር ይልቅ የጥላቻ አስተሳሰብን የሚያራምዱና የሚዲያን መርሕ መሠረት አድርገው የማይናገሩ አካላትን ወደሚዲያቸው በማምጣት በሕግ ከተቀመጠው ገደብም አልፈው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለሦስት ሺህ ዘመናት ታፍራና ተከብራ በኖረችበት ሀገሯ ከዶግማዊ ቀኖናዊና ትውፊታዊ አስተምህሮዋ ውጭ የሆኑ የአስተምህሮዋንም ባሕርይ ፈጽመው የማያውቁ ግልሰቦች ከአስተምህሮዋ በተቃራኒ ስለቆሙ ወይም እርሷ ከአስተምህሮአቸው በተቃራኒ ስለሆነች እንዲህ ዓይነቱን ከእውነታው ጋር ፍጹም ተቃራኒ የሆነ ትችትን ነቀፌታንና ሃይማኖታዊ ክብርን የሚጋፉ ንግግሮችን እንዲናገሩ የሚያደርጉ፣  የአንዲትን ታላቅ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ በአላዋቂዎችና በተቃራኒ ጎራ በተሰለፉ ግልሰቦች የሚያስተቹ  የሚዲያ ባለቤቶች እንደዚሁም ተጋባዥ ግለሰቦቹ በሕግ ሊጠየቁ ይገባል፡፡

ከሐምሌ ወር ፳፻፲ ዓ.ም በሶማሌ ጅግጅጋ በቤተክርስቲያንና በኦርቶዶክሳውያን ላይ ከተደረገው የጥፋት ዘመቻ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ በሀገራችን ልዩ ልዩ አካባቢዎች በቅድስት ቤተክርስቲያንና በኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ላይ እየተፈጸመ ያለው አሰቃቂ ጥቃት ለዚህ ዓይነተኛ ማሳያ ነው፡፡

ገዢ ሕግና ሕገ መንግሥት ጨዋ ሕዝብና አስተዋይ ምሁራን ያሏትን ሀገር ምራቃቸውን ያልዋጡ ጽንፈኞች በመንጋ እየፈረዱ ሰላማውያን የሆኑ ምእመናን ወገኖቻችንን በመንጋ ሲያርዱ አብያተ ክርስቲያናትንም ሲያቃጥሉ ሰላምና ፀጥታ አስከባሪው በጥቃት ወቅት አካል በሀገር ውስጥ የሌለ እስኪመስል ድረስ የሚደርሰው የነደደ እስትን ለማጥፋት አለዚያም የሞተውን አስከሬኑን ለማንሣት ነው፡፡ አራጆች ተይዘው በሕግ ፊት ለፍርድ አይቀርቡም ፍትሕና የሕግ የበላይነትም ሥፍራቸውን ለመንጋ ፈራጆች ትተዋል፡፡ በመጽሐፍ ‹‹እግዚአብሔር ሀገርን ካልጠበቀ ጠባቂዎች በከንቱ ይደክማሉ›› ተብሎ እንደተነገረ የሀገርን ደኅንነትና ፀጥታ በማስጠበቅ ከእንደዚህ ዓይነቱ የመንጋ ጥቃትም ሀገርን ይጠብቃል ሕዝብንም ከጥፋት ይታደጋል ተብሎ እምነት የተጣለበት ሕዝባዊ ፖሊስና የመከላከያ ኃይል እግዚአብሔር ሀገርን ካልጠበቀ የጠባቂዎች ድካም ሁሉ ከንቱ መሆኑን በዚህ ዘመን በትክክል አይተንበታል፡፡
በተለይም አንዳንድ የፖሊስ አካላት የተሠጣቸውን ሕዝባዊ አደራ በመዘንጋት ከሀገር ይልቅ ብሔርንና ሃይማኖታዊ ጎጠኝነትን በማስቀደም ፀጥታን የማስከበር ፍትሕንም የማስጠበቅ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ባለመወጣታቸው ምክንያት ማኅበረሰቡ በፖሊስና በሌላው የፀጥታ አካላት ላይ እምነት እንዳይኖረው አድርጎታል፡፡ ከዚህም የተነሣ በአካባቢው ጥቃት በሚፈጸምበት ወቅት ወደ ፀጥታ አካላት ሄዶ የድረሱልኝ ከማሰማት ይልቅ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሸሽ በዚያ መጠለልን እየመረጠ ይገኛል፡፡

የሀገሪቱን ልዩ ልዩ አካባቢዎች ትኩረት አድርጎ ከቋንቋ ወደ ብሔር ከብሔር ደግሞ ወደ ቋንቋ ሲዛመት የሰነበተው የግጭት ወረርሽኝ በሰሞንኛው የጥቃት ሰለባ ደግሞ ትኩረቱን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ላይ በማድረግ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚማሩ ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎችን ተረኛና የጥቃቱ ዒላማዎች አድርጓቸው ሰንብቷል፡፡ መነሻውን በወልድያ ዩኒቨርሲቲ ያደረገው ይህ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ግጭት በሀገሪቱ በተለይም በኦሮምያ ክልል በሚገኙ በርካታ ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ ተማሪዎችን የጥቃት ሰለባ አድርጓቿል፡፡ ግጭቱ ከመጀመሪያው ብሔር ተኮር ይዘት ያለው ቢመስልም በስተኋላ ግን ትኩረቱን ሙሉ በሙሉ ወደ ሃይማኖት ቀይሮ ለበርካታ ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎች ሕይወት መጥፋትና አካል መጉደል ከትምህርት ገበታቸውም መፈናቀል ምክንያት ሆኗል፡፡ ወላጆችም ስንቅ ሰንቀው የላኳቸውን ልጆቻቸውን ተምረው ተመርቀው ይመጣሉ ሲሉ ነገሩ ከታሰበው በተቃራኒው ሆኖ አስከሬናቸው እንዲመለስላቸው አድርጓቸዋል፡፡

የሀገርንና የሕዝብን ደኅንነት የመጠበቅና የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለበት መንግሥት ሀገር የሆነችው ‹‹ኦርቶዶክስ›› ስትጠፋ ካህናትና ምእመኖቿ የጥፋት ኃይሎች ዒላማ ሆነው በዐደባባይ በእሳት ሲቃተሉ በሰይፍ ሲታረዱ ለዘመናት ያፈራቻቸው ኪነ ሕንፃዎቿ ቅርሶቿና የከበሩ ንዋያተ ቅድሳቶቿ በወንበዴዎች ሲዘረፉና ሲወድሙ መንግሥት የሆነውንና የሚሆነውን ሁሉ እያየ እየሰማ በደብዳቤም ሆነ በአካል እየተነገረው፣ በኦርቶዶክሳዊ ሰልፎቿና በጋዜጣዊ መግለጫዎቿ ያስተላለፈቻቸውን ጥብቅ መልእክቶችም ሆነ ያሰማቻቸውን የድረሱልኝ ጩኸቶች አስቸኳይ ጉዳዩ በማድረግ ከሚደርስባት መከራ ሊታደጋት ፈጽሞ አልተቻለውም፡፡

አባቶቻችን መንግሥት ባልነበረበት ዘመን የቀደመ ልዕልናዋን በማስጠበቅ ታፍራና ተከብራ እንዲትኖር ያደረጓትን ቤተ ክርስቲያንን ዛሬ ሀገርንና ሕዝብን እያስተዳደረ ያለ መንግሥት የዚችን ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ደኅንነት ማስጠበቅ ከተሳነው፤ በጽንፈኛ ወራሪዎች በየዐደባባዩ እንደ በግ የሚታረዱትን የምእመናንን ሕይወትም ከሞት መታደግ ከልተቻለው ‹‹እረኛው በጎችን መጠበቅ ከተሳነው በጎች እርስ በእርሳቸው ይጠባበቃሉ›› እንዲሉ ከዚህ በኋላ ኦርቶዶክሳውያን በተጠናከረ ኃይል ተደራጅተው እርስ በእርሳቸው መጠባበቅ ይኖርባቸዋል፡፡ በዚህ ሰዓት ብቸኛ መፍትሔ የሚሆነውም ይህ ብቻ ነውና፡፡ ምእመናን የእግዚአብሔርን ቤተመቅደስና ንዋያተ ቅድሳቱን ሁሉ ነቅተን መጠበቅ እንዳለብን በመጽሐፍ ‹‹የማደሪያውን ሥራ ይሠሩ ዘንድ የመገናኛውን ድንኳን ዕቃ ሁሉ ይጠብቁ›› እንደዚሁም ‹‹መቅደሱንና መሠዊያውን ጠብቁ… እንደዚሁም ወንዶችሁሉ እንደ ቁጥራቸው… መቅደሱን ይጠብቁ ነበር›› ተብሎ የተጻፈው የእግዚአብሔር ቃል የሚያስተምረን ይህንን ነው፡፡ (ዘኁ.፫፥፰-፳፰)

የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ነቅቶ የመጠበቅ ድርሻ ለምእመናን ብቻም ተለይቶ የተሰጠም እንዳልሆነም አባቶቻችን ካህናትም በቤተመቅደሱ ከትመው በንቃት የመጠበቅ ድርሻ እንዳለባቸው ‹‹ሌዋውያን በምስክሩ ማደሪያ ዙሪያ ይሥፈሩ የምስክሩን ማደሪያም ይጠብቁ›› የሚለው የእግዚአብሔር ቃል ይነግረናል፡፡ (ዘኁ.፩፥፶፫)

ዛሬ ላይ በኵራት አሉን የምንላቸው የከበሩ ንዋያተ ቅድሳትና የብራና ቅዱሳት መጻሕፍት አባቶቻችን በቀደሙት የቤተክርስቲያን የመከራ ዘመናት በዱር በገደል በዋሻ በፍርኩታ በባሕር ውስጥና በከርሠ ምድርም ሳይቀር በመሠወር ጠብቀው ስላቆዩልን ነው፡፡ ስለሆነም የዘመናችንም ምእመናንና ካህናት የቀደሙትን አባቶቻችንን እምነትና ጥንካሬ አርአያ፣ ረድኤተ እግዚአብሔርንም አጋዥ በማድረግ ቅድስት ቤተክርስቲያንና የከበሩ ንዋያተ ቅድሳቷን ከጽንፈኛ ኃይሎች ለመታደግ እስከ ሞት ድረስ መሥዋዕትነትን በመክፈክ ለመጪው ትውልድ በክብር ማስተላለፍ አለብን፡፡

ምንጭ፡-ስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ ኅዳር ፳፻፲፪ ዓ.ም.
https://t.me/yeberhanljoche
Forwarded from Acorns
💵ስልኮን በመጠቀም በወር እስከ 10,000 ብር በላይ ተከፋይ ይሁኑ 😱

🔅የ Acorns ቦት ጋር ልክ እንደገቡ የ 100 ብር ስጦታ ያገኛሉ በተጨማሪም 1 ሰዉ ወደ ቦቱ ሲጋብዙ በየቀኑ የ 50 ብር ቋሚ ክፍያ


🔥ይህ የእርሶ የመጋበዣ link ነው ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ 👇👇
https://t.me/FreeEearnMoneyPay_Bot?start=r0475648302
#ሰበር_ዜና

ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው እለት በአካሔደው ምርጫ ብፁዕ አቡነ አብርሃምን የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስን የቅዱስ ዋና ጸሐፊ በማድረግ ሾሟል።

የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከእነሱ ጋራ ይኹን!
@yeberhanljoche
✔️ዕርገት እንኳን አደረሰን

⛪️ዐረገ እግዚአብሔር በይባቤ ፤ወእግዚእነ በቃለ ቀርን፤ ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ።///" አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ። ዘምሩ፥ ለአምላካችን ዘምሩ፤ ዘምሩ፥ ለንጉሣችን ዘምሩ።"

✝️" ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተናገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ።" ማር ፲፮፥፲፱

✍️"እናንተም ለዚህ ምስክሮች ናችሁ። እነሆም፥ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ# ኃይል #እስክትለብሱ ድረስ #በኢየሩሳሌም #ከተማ ቆዩ። እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው። ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ #ሰማይም #ዐረገ። እነርሱም፤ ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፥ ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ።" ፳፬፥፵፰-፶፫

"ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ኢየሱስ የመረጣቸውን ሐዋርያትን በመንፈስ ቅዱስ ካዘዛቸው በኋላ እስከ ዐረገበት ቀን ድረስ፥ ያደርገውና ያስተምረው ዘንድ ስለ ጀመረው ሁሉ መጀመሪያውን ነገር ጻፍሁ፤ ደግሞ አርባ ቀን እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው። ከእነርሱም ጋር አብሮ ሳለ ከኢየሩሳሌም እንዳይወጡ አዘዛቸው፥ ነገር ግን። ከእኔ የሰማችሁትን አብ የሰጠውን የተስፋ ቃል ጠብቁ፤ ዮሐንስ በውኃ አጥምቆ ነበርና፥ እናንተ ግን ከጥቂት ቀን በኃላ በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ አለ። ሐዋ ሥራ ፩፥፩-፭


በችግር ላይ ያሉትን እሱ በምህረቱ ይዳብስልን
https://t.me/yeberhanljoche
ኦርቶዶክሱ ቅዱሳንህን እወቅ

አቡነ ዜና ማርቆስ

ቀድሰው ሕዝቡን ሁሉ ሲያቆርቡ ቢመሽባቸው ፀሐይን እንደ ኢያሱ ገዝተው ያቆሟት እና 8 እንጀራን አበርክተው 8ሺህ ሕዝብ በመመገብ ጌታችንን የመሰሉት ታላቁ ጻድቅ አቡነ ዜና ማርቆስ

አቡነ ዜና ማርቆስ፡- አባታችን ዜና ማርቆስ ሀገራቸው ጽላልሽ አውራጃ ምድረ ዞረሬ ስትሆን ትውልዳቸው ከነገደ ሌዊና ከእስራኤል ነገሥት ወገን ነው፡፡ ወላጆቻቸው ልጅ በማጣት ሲያዝኑ አንድ ዕለት ሐዋርያውና ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ወደ እናታቸው ማርያም ዘመዳ ሌሊት መጥቶ ገድሉና ትሩፋቱ በዓለም ሁሉ የመላ ጻዲቅ ልጅ እንደምትወልድ ነገራት፡፡ ለአባቱ ለቀሲስ ዮሐንስም እንዲሁ ተገልጦለት ‹‹ሚስትህ ማርያም ዘመዳ የካቲት 24 ፀንሳ ኅዳር 24 ቀን ይኸውም በካህናተ ሰማይ በዓል ቀን ትወልዳለች፣ ስሙም ዜና ማርቆስ ይባላል›› በማለት ብስራቱን ነግሮታል፡፡

በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ብሥራት መሠረት አባታችን በተወለዱም ዕለት ቅዱስ ዑራኤልና ቅዱስ ሩፋኤል የብርሃን ልብስ አልብሰው በክንፋቸው ሲጋርዱአቸው ለሰዎችም ሁሉ ታይቷል በወቅቱም የአባ ሳሙኤል ዘወገግ አባት እንድርያስና የአቡነ ተክለሃይማኖት አባት ቅዱስ ጸጋ ዘአብ እስኪደነቁ ድረስ ይህን በዓይናቸው ተመልክተዋል፡፡ ሁለቱ መላእክትም ከእናታቸው ዕቅፍ ወስደው ወደ ሐዋርያው ማርቆስ መቃብር ወስደው ለማርቆስና ለቅዱሳን ጳጳሳት አስባርከዋቸው መልሰው ለእናቱ ሰጧቸው፣ እናቱ ግን ይህን አታውቅም ነበርአቡነ ዜና ማርቆስም በተወለዱ በሦስተኛው ቀን በእግራቸው ቆመው ‹‹አንድ አምላክ ለሆኑ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ እሰግዳለሁ›› ብለው ሦስት ጊዜ አምላካቸውን አመስግነው ሰግደዋል፡፡ በ40 ቀኑ ሲጠመቅ የሚያጠምቀው ካህን የአባቱ ወንድም እንድርያስ ውኃው ሲፈላ አይቶ ሸሽቷል፡፡ መልአኩም እንዳይፈራ ነግሮት ለእርሱም ተአምር እንደሚደረግለት አስረዳው እንድርያስም ዕድሜው 72 ነበርና ራሰ በራ ስለነበር በውኃውም ራሱን ቢታጠብበት ጸጉር አብቅሏል፡፡ ሕዝቡም ሁሉ ይህን አይቶ አደነቀያችም ውኃ ሌሎች በጣም ብዙ ተአምራትን አደረገች፡፡

አንድ ዓመት በሆነውም ጊዜ ቤተክርስቲያን ውስጥ እየዳኸ ሲሄድ መልአክ በክንፎቹ አቅፎ ወስዶ ጌታችንና እመቤታችን ጋር አቅርቦት አስባርኮታል፡፡ እንዲሁም የ15ቱን ነቢያት፣ የ12ቱን ሐዋርያት የ72ቱን አርድእት፣ ሃይማኖታቸው የቀና የ318ቱን ሊቃውንት፣ የጻድቃንን፣ የሰማዕታትን የእነዚህን ሁሉ በረከት እንዲቀበል ካደረገው በኋላ ወደዚያች ቤተክርስቲያን መለሰው፡፡ ከጳጳሱ ከአቡነ ጌርሎስ ድቁናን ተቀብሎ ከአባቱ ጋር ወደ ሀገሩ ሲመለስ ዘራፊዎች ደብድበው በትራቸውንም ሳያስቀሩ ዘረፏቸውአቡነ ዜና ማርቆስም ወደ ፈጣሪው በጸለየ ጊዜ በትራቸው እባብ ሆና ነድፋ ገደለቻቸው፡፡ በኋላም ወደ አምላካቸው ጸልየው ከሞት እንዲነሱ በማድረግ በአካባቢውም ያሉ ሰዎች ሁሉ በእርሱ አምላክ እንዲያምኑ አድርጓቸዋል

‹አቤቱ ጠላቶቹን እስከደመሰሰና ለእስራኤል ልጆች ርስታቸውን እስካካፈለ ድረስ ለኢያሱ ፀሐይን በገባዖን ያቆምክ አንተ ነህ፤ ዛሬም ቅዱስ ሥጋህን ክቡር ደምህን ለእነዚህ ባሮችህ ቅዱሳን መነኮሳትና ለሕዝቦችህ እስከማቀብላቸው ድረስ እንዲሁ በቸርነትህ ብዛት ፀሐይን አቁማት› ብሎ በጸለየ ጊዜ ፀሐይዋ ወዲያውኑ ቆመች፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዳሴውን ጨርሶ ሕዝቡን ሁሉ አቆረባቸው፡፡››

ቅዱስ አባታችን በምሁር ኢየሱስ ገዳም ከሬብ በሚባል ዋሻ ውስጥ 40 ዓመት ዘግተው ተጋድለዋል፡፡ በዚህም ሳሉ መልአክ የዕረፍታቸውን ዕለት ታኅሣሥ ሦስት ቀን እንደሚሆን ስለነገራቸው ታኅሣሥ አንድ ቀን ወደ ገዳማቸው በመሄድ ቀድሰው ሕዝቡን ሁሉ ሲያቆርቡ ቢመሽባቸው ፀሐይን ለሁለተኛ ጊዜ እንደ ኢያሱ ገዝተው አቁመዋታልአባታችን ዜና ማርቆስ የዕረፍታቸውን ዕለት ከመልአኩ ከተረዱ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አሏቸው፡- ‹‹ከዚህ ዓለም የምለይበት ጊዜ ደርሷልና ወደ ፈጣሩዬ እሄዳለሁ፣ እኔ ሽማግሌ አባታችሁ የምመክራችሁን ስሙ፣ ከበጎ ሥራ ሁሉ አስቀድማችሁ እርስ በእርሳችሁ ተዋደዱ፣ ፍቅር ሰማያዊ መንግሥትን ለማግኘት በባለሟልነት ወደ እግዚአብሔር ፊት ያደርሳልና›› ብለው መከሯቸው፡፡ ዳግመኛም ጾመኛ ነኝ አትበሉ አሏቸው፡፡ ‹‹ስለ ነፍሳችሁ ድኅነት፣ ከመከራና ከጥፋትም ሁሉ ለማምለጥ በምትጾሙ ጊዜ እንዲህ እየጾማችሁ ሳላችሁ ስለምትሹትግብር ወደ ዓለም ሰዎች ብትደርሱና በጾም ቀን ሲበሉና ሲጠጡ ብታዩአቸው መብልና መጠጥን በሚወዱ ሰዎች ፊት በውጭ በአደባባይ ‹ዛሬ የጾም ቀን ስለሆነ እኛ እንጾማለን› አትበሉ፡፡ ስለ እናንተ መጾምና ስለ እነርሱም አለመጾም አንዳች አትናገሩ፣ ባለመጾማቸውም አትንቀፏቸው፡፡ ስለ ሌላ ሥራ ወደማይጾሙ ሰዎች ብትደርሱ ግን በጾም ዕለት ወንድሞቻችን ‹ኑ አብረን እንብላ› ቢሏችሁ እኛ እንጾማለን አትበሉ፣ እንዲህ በሉ እንጂ፡- ‹ወደ እናንተ ከመምጣታችን በፊት ከቤት በልተናል፣ ጠግበናል› ስትሏቸው እናንተ እንደምትጾሙ ያውቃሉ፡፡›››

ከዚህም በኋላ አቡነ ዜና ማርቆስ ታኅሣሥ ሁለት ቀን የደቀ መዛሙርቶቻቸውን እግር ሲያጥቡ ውለው አስቀድሞ መልአኩ እንደነገራቸው ታኅሣሥ ሦስት ቀን በ140 ዓመታቸው ነቢይም፣ ሐዋርያም፣ ካህንም፣ ባለራእይም፣ የሀገራችንም ብርሃን የሆኑት ጻዲቁ አባታችን በክብር ዐርፈዋል ጌታ ለአባታችን ብዙ ቃልኪዳን የገባላቸው ሲሆን ከቃልኪዳናቸው ውስጥ እሚገርመኝ አንዱ ይህ ነው ማንም 1 ጧፍ ወደ ገዳምህ ይዞ መጥቶ የሰጠ ሰው ቢኖር ከአገሩ ከወጣ ወደ ሀገሩ ሳልመልሰው እና ንስሀ ገብቶ ሳይቆርብ አይሞትም የሚል ነው እንዲሁም በስምህ ቢለምነኝ ስለ ወዳጄ ስለ አንተ ስል ከ160 ዓመት ወይም ከ140 ወይም ከ120 ወይም 80 ዓመቱ በፊት በሞት አልወስደውም። እነዚህን ዕድሜ እንዲያይ አደርሰዋለው፤ እነዚህንም ዓመታት እየጨመርኩኝ ዘመኑን በመልካም እንዲፈፅም
እጠብቀዋለው።
የአቡነ ዜና ማርቆስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
https://t.me/yeberhanljoche
✟የዕለት እንጀራችንን ስንቀበል የአደራውንም መስጠት አንዘንጋ✟

በጸሎት ኃይል የሚያምን አንድ ጽኑዕ ክርስቲያን ነበር፡፡ ይህም ክርስቲያን ጥሪት የሌለው ደሃ፣ የሚበላ የሚቸግረው ረሃብተኛ፣ ልብሱ በላዩ ላይ አልቆ የታረዘ ምስኪን ነው፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በጸሎት ሕይወቱ የነበረውን ትጋት በቅርበት ያውቅ የነበረው አንድ ወዳጁ እየተቆጣ ‹ቢያንስ ለረሃብህ ማስታገሻ ቁራሽ ዳቦ እንኳን ማሰጠት ካልቻለ የአንተ ጸሎት ፋይዳው ምንድር ነው? ይቅርብህ በቃ! ፈጣሪህ አይሰማህም ማለት ነው› ሲል ተስፋ በሚያስቆርጥ ቃል ተናገረው፡፡ ያም ምስኪን ክርስቲያን እንዲህ ሲል መለሰለት :- ‹እግዚአብሔርማ አልረሳኝም። ለአንዱ ሰው ከዕለት እንጀራው የበለጠ አትርፎ በመስጠት ለእኔ እንዲያካፍለኝ መልእክተኛ አድርጎት ነበር፡፡ነገር ግን ይህን አደራ የተቀበለው ሰው ዘነጋኝ፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ሳይሆን አድራሹ ሰው ረስቶኛል!›

መጻሕፍት እንደሚያስተምሩን "የዕለት እንጀራችንን ስጠን" የሚለው ጸሎት ለመነኮሳት ሲሆን "ለዕለት"፣ በዓለም ለሚኖሩ ሰዎች ሲሆን ደግሞ "ለዓመት" የሚሆን እንጀራ ስጠን ማለት ነው። ታዲያ ለምን አንዳንዶች ከዓመት የሚተርፍ ብዙ እንጀራ ሲያገኙ፣ ሌሎች ደግሞ ለዕለት እንኳን የሚሆን ቁራሽ ያጣሉ ? መቼም ‹ለሰው ፊት የማያዳላ› እግዚአብሔር "አድልዎ ቢኖርበት ነው" ብለን የድፍረት ቃል በእርሱ ላይ አንናገርም።(ሐዋ 10፥34) ይህ የሆነው እንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርት አትርፈው ያገኙ ሰዎች ምንም የሌላቸውን እንዲረዱ እና መግቦት የባሕርይው የሆነውን አምላካቸውን በጸጋ እንዲመስሉት ነው። በዚሁም ላይ በፈጠራቸው ሰዎች መካከል ያለውን የመተዛዘንና የፍቅር ትስስር የበለጠ ለማጠናከር ነው፡፡

‹የዕለት እንጀራችንን ስጠን ለዛሬ› ብለን የለመንነው አምላክ ከዓመት እንጀራችን በላይ አትርፎ የሚሰጠን፣ የሚበቃንን ያህል ተመግበን በቀረው ለሌሎች አድራሽ መልእክተኞች እንድንሆን ነው። ስለዚህ ይህን የተጣለብንን አምላካዊ አደራ ባለመወጣት ድሆችን አንበድል፤ ተማርረው ከፈጣሪያቸውም ጋር እንዲጣሉ አናድርጋቸው።
@yeberhanljoche