ውሉደ ብርሀን ሰ/ት/ቤ/ት🙏(ጫንጮ)
766 subscribers
84 photos
4 files
98 links
ሰንበት ትምህርት ቤት የመልካም ወጣት የመልካም ትውልድ መፍለቂያ ናት! ትውልድን ለበጎ ነገር የምታበቃ ናት፡፡


የጫንጮ ከተማ ደ/ብ/ቅ/እግዚአብሔር አብ እና ደ/ሲ/ቅ/ ኪዳነ ምህረት ቤ/ክ ው/ብ/ሰ/ት/ቤት ቻናል
ለሀሳብ እና አስታየት @weldebirhanbot @ty1921 ይጠቀሙ

ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ መልካም ነው፡፡
Download Telegram
💠 #ኢየሱስ_ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነው። 💠

✧ በወንጌልም ሆነ በተለያዩ የሀዲስ ኪዳን የመልእክት ክፍሎች ውስጥ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ተጠቅሶ ይገኛል። እንደውም ማንኛውም ክርስቲያን፥ ኢየሱስ እግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ማመን መቀበል እንዳለበት አጽንኦት ተሰጥቷል፡፡

✧ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቂሳርያ ሀዋርያቱን ሰብስቦ ሰዎች ማን እንደሚሉት በጠየቃቸው ጊዜ አንዳንዶች ኤልያስ ከነብያት አንዱ እንደሆነ እንደሚናገሩ ሲነግሩት እናንተ ማን እንደሆንኩ ትላላችሁ ብሎ ቢጠይቃቸው ክርስቶስ የህያው እግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ቅዱስ ጴጥሮስ ተናግሯል ጌታችንም ቅዱስ ጴጥሮስን አመስግኖ ስጋና ደም እንዳልገለጠለት የሰማዩ አባቱ እንደገለጠለት በመናገር በዚህ በቅዱስ ጴጥሮስ ንግግር ቤተክርስቲያኑን እንደሚመሰርት ጌታ ተናግሯል ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው የሚለው የቅዱስ ጴጥሮስ ንግግር የቤተክርስቲያን መሰረት ነው። የጌታን ማንነት የሚገልጽ እምነታችን መሰረት ነው፡፡

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ የማያምን እንዲሁም ብሎ የማይመሰክር ሰው ክርስቲያን ተብሎ ሊጠራ አይችልም ምክንያቱም የክርስትና መሰረት ይህ ስለሆነ ‹‹ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን። ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ። እርሱም፦ አንዳንዱ #መጥምቁ_ዮሐንስ ፥ ሌሎችም #ኤልያስ ፥ ሌሎችም #ኤርምያስ ወይም #ከነቢያት_አንዱ ነው ይላሉ አሉት።
እርሱም፦ #እናንተስ #እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው።
ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ፦ #አንተ #ክርስቶስ_የሕያው_እግዚአብሔር_ልጅ ነህ አለ። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ #በሰማያት ያለው #አባቴ እንጂ #ሥጋና #ደም ይህን #አልገለጠልህምና #ብፁዕ ነህ። እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም። የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል።››ማቴ 16፡13-19

ቅዱስ ገብርኤልም እመቤታችንን ለማብሰር በተላከ ጊዜ ከእርሷ የሚወለደው <<ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ>> እንደሚባል ነግሯታል እሷም ይህንን በእምነት ተቀብላ ስግው ቃል/ሰው የሆነ አምላክ/ እግዚአብሄርን በስጋ ወልዳዋለች ስለዚህም ወላዲተ አምላክ ብለን እንጠራታለን፡፡ የሉቃስ ወንጌል 1፡35 ‹‹መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት፦ መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።››

✧ በተለያየም ቦታ አጋንንት እኳን ሳይቀሩ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መስክረዋል፡፡ ማቴ 8፡29 አይሁድም የእምነታችን መሰረት የሆነውን የእግዚአብሔር ልጅነቱን አልተቀበሉም ነበር፡፡ማቴ 26፡63 ይዘብቱበትም ነበር ማቴ 27፡43 ፡፡ ቅዱስ ማርቆስም ወንጌሉን ሲጀምር እግዚአብሔር ልጅነቱን መስክሮ ነው ማር1፡1፡፡ በተለያየ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል ክፍል ውስጥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑ ተጠቅሷል ይህንንም እናመን ዘንድ ወንጌል እንደተፃፈ ይነግረናል ዮሐ 1፡34 ፤1፡50 ፤6፡69 ፤ 10፡36 ፤11፡4 ፤11፡27 ፤ 19፡7 ፤ 20፡31፡፡

✧ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ይህንን አምኖ እንደተጠመቀ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል ሐዋ 8፡37፡፡ቅዱስ ዮሐንስ በመልእክቱም ኢሱስ የእግዚአብሄር ልጅ እንደሆነ ተናግሯል ‹‹ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በሚታመን ሁሉ እግዚአብሔር በእርሱ ይኖራል እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል።››1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4፡15፡፡

እንግዲህ ከላይ እንደተመለከትነው መጽሀፍቅዱስ አፅንኦት ሰጥቶ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በእግዚአብሔር ልጅነቱም ማመን እንዳለብን ይናገራል...

??? ለመሆኑ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ሲባል ምን ማለት ነው ???

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ሲባል መፅሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን እግዚአብሔር ነው ማለት ነው። እኛ የሰው ልጆች ሰዎች እንደምንባል ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ኢየሱስም እግዚአብሔር ተብሎ ይጠራል፡፡ ኢየሱስ እግዚአብሔር ነው ሲባል አብን በመልክ የሚመስለው በባህሪ የሚስተካከለው ማለታችን ነው ዮሐ 1፡1-3 ፤ ዮሐ 10 ፡30 ፤ዮሐ 14፡8-10 ‹‹እኔና አብ አንድ ነን እኔን ያየ አብን አይቷል››፡፡ ልጅነቱም የባህሪ ልጅነት ነው ማለትም ከማንም ያልተቀበለው ማንም የማይወስድበት ዘላለማዊ ልጅነት ነው፡፡

✧ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የአብ ልጅ እንደሆነ ከአብ ጋር አንድ እንደሆነ እና አብ የሚያደርገውን ሁሉ እንደሚያደርግ ለአይሁድ ሲነግራቸው ድንጋይ አንስተው ሊወግሩት በማሰባቸው ጌታችን ስለምን ትወግሩኛላቻሁ ባላቸው ጊዜ ስለመልካም ስራህ አንወግርህም ስለስድብህ ነው ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለማድረግህ ነው ማለታቸው በወንጌል ተመዝግቧል እንግዲህ አይሁድ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ማለቱ አምላክ ነኝ ማለቱ እንደሆነ ገብቷቸዋል ማለት ነው ዮሐ 10፡25-38

✧ ከዚህ ጥቅስ እንደምንረዳው ጌታችን ራሱን የእግዚአብሔር ልጅ ብሎ መጥራቱ አምላክ ነኝ ማለቱ እንደሆነ ነው/ ሙሉውን የአይሁድ እና የጌታን ንግግር አንብቡት/፡፡በሌላም ቦታ አይሁድ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎ ራሱን መጥራቱን ተቃውመው ሊገሉት እንደነበር የእግዚአብሄር ልጅ ነኝ ማለቱ ደግሞ እግዚአብሔር ነኝ ማለቱ እንደሆነ ተረድተውት ሊገሉት እንደሚፈልጉ ተገልጧል ‹‹እንግዲህ ሰንበትን ስለ ሻረ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ደግሞ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካክሎ <<
እግዚአብሔር አባቴ ነው ስላለ፥ ስለዚህ አይሁድ ሊገድሉት አብዝተው ይፈልጉት ነበር።››ዮሐ 5፡18

✧ ስናጠቃልለው ኢየሱስ እግዚአብሔር ልጅ ተብሎ መጠራቱ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደተመለከትነው አምላክ/እግዚአብሔር መሆኑን የሚገልጥልን ልጅነቱም ከማንም ያልተቀበለው ባህሪ ልጅነት እንደሆነ እግዚአብሄርንም የሚስተካከልበት ልጅነት በመልክ ሚመስልበት ልጅነት እንደሆነ ልንረዳ ያስፈልጋል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ሰላም የተዋህዶ እምነት ተከታዮች በሙሉ🙏

ከዛሬ ጀምሮ በአዲሱ ቻናላችን ስለ ሰ/ት/ቤቱ መረጃዎች እንዲሁም ስለተዋህዶ ሀይማኖት እየፃፍን እናቀርባለን።
ጎደኛዎትን ለመጋበዝ ከፈለጉ ከታች የለዉን ሰማያዊ ሊንክ ሼር በማድረግ አባልነቶን ያሳዩን።

@yeberhanljoche @yeberhanljoche
@yeberhanljoche @yeberhanljoche
💠 #ኢየሱስ_ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነው። 💠

✧ በወንጌልም ሆነ በተለያዩ የሀዲስ ኪዳን የመልእክት ክፍሎች ውስጥ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ተጠቅሶ ይገኛል። እንደውም ማንኛውም ክርስቲያን፥ ኢየሱስ እግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ማመን መቀበል እንዳለበት አጽንኦት ተሰጥቷል፡፡

✧ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቂሳርያ ሀዋርያቱን ሰብስቦ ሰዎች ማን እንደሚሉት በጠየቃቸው ጊዜ አንዳንዶች ኤልያስ ከነብያት አንዱ እንደሆነ እንደሚናገሩ ሲነግሩት እናንተ ማን እንደሆንኩ ትላላችሁ ብሎ ቢጠይቃቸው ክርስቶስ የህያው እግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ቅዱስ ጴጥሮስ ተናግሯል ጌታችንም ቅዱስ ጴጥሮስን አመስግኖ ስጋና ደም እንዳልገለጠለት የሰማዩ አባቱ እንደገለጠለት በመናገር በዚህ በቅዱስ ጴጥሮስ ንግግር ቤተክርስቲያኑን እንደሚመሰርት ጌታ ተናግሯል ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው የሚለው የቅዱስ ጴጥሮስ ንግግር የቤተክርስቲያን መሰረት ነው። የጌታን ማንነት የሚገልጽ እምነታችን መሰረት ነው፡፡

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ የማያምን እንዲሁም ብሎ የማይመሰክር ሰው ክርስቲያን ተብሎ ሊጠራ አይችልም ምክንያቱም የክርስትና መሰረት ይህ ስለሆነ ‹‹ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን። ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ። እርሱም፦ አንዳንዱ #መጥምቁ_ዮሐንስ ፥ ሌሎችም #ኤልያስ ፥ ሌሎችም #ኤርምያስ ወይም #ከነቢያት_አንዱ ነው ይላሉ አሉት።
እርሱም፦ #እናንተስ #እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው።
ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ፦ #አንተ #ክርስቶስ_የሕያው_እግዚአብሔር_ልጅ ነህ አለ። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ #በሰማያት ያለው #አባቴ እንጂ #ሥጋና #ደም ይህን #አልገለጠልህምና #ብፁዕ ነህ። እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም። የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል።››ማቴ 16፡13-19

ቅዱስ ገብርኤልም እመቤታችንን ለማብሰር በተላከ ጊዜ ከእርሷ የሚወለደው <<ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ>> እንደሚባል ነግሯታል እሷም ይህንን በእምነት ተቀብላ ስግው ቃል/ሰው የሆነ አምላክ/ እግዚአብሄርን በስጋ ወልዳዋለች ስለዚህም ወላዲተ አምላክ ብለን እንጠራታለን፡፡ የሉቃስ ወንጌል 1፡35 ‹‹መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት፦ መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።››

✧ በተለያየም ቦታ አጋንንት እኳን ሳይቀሩ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መስክረዋል፡፡ ማቴ 8፡29 አይሁድም የእምነታችን መሰረት የሆነውን የእግዚአብሔር ልጅነቱን አልተቀበሉም ነበር፡፡ማቴ 26፡63 ይዘብቱበትም ነበር ማቴ 27፡43 ፡፡ ቅዱስ ማርቆስም ወንጌሉን ሲጀምር እግዚአብሔር ልጅነቱን መስክሮ ነው ማር1፡1፡፡ በተለያየ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል ክፍል ውስጥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑ ተጠቅሷል ይህንንም እናመን ዘንድ ወንጌል እንደተፃፈ ይነግረናል ዮሐ 1፡34 ፤1፡50 ፤6፡69 ፤ 10፡36 ፤11፡4 ፤11፡27 ፤ 19፡7 ፤ 20፡31፡፡

✧ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ይህንን አምኖ እንደተጠመቀ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል ሐዋ 8፡37፡፡ቅዱስ ዮሐንስ በመልእክቱም ኢሱስ የእግዚአብሄር ልጅ እንደሆነ ተናግሯል ‹‹ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በሚታመን ሁሉ እግዚአብሔር በእርሱ ይኖራል እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል።››1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4፡15፡፡

እንግዲህ ከላይ እንደተመለከትነው መጽሀፍቅዱስ አፅንኦት ሰጥቶ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በእግዚአብሔር ልጅነቱም ማመን እንዳለብን ይናገራል...

??? ለመሆኑ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ሲባል ምን ማለት ነው ???

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ሲባል መፅሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን እግዚአብሔር ነው ማለት ነው። እኛ የሰው ልጆች ሰዎች እንደምንባል ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ኢየሱስም እግዚአብሔር ተብሎ ይጠራል፡፡ ኢየሱስ እግዚአብሔር ነው ሲባል አብን በመልክ የሚመስለው በባህሪ የሚስተካከለው ማለታችን ነው ዮሐ 1፡1-3 ፤ ዮሐ 10 ፡30 ፤ዮሐ 14፡8-10 ‹‹እኔና አብ አንድ ነን እኔን ያየ አብን አይቷል››፡፡ ልጅነቱም የባህሪ ልጅነት ነው ማለትም ከማንም ያልተቀበለው ማንም የማይወስድበት ዘላለማዊ ልጅነት ነው፡፡

✧ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የአብ ልጅ እንደሆነ ከአብ ጋር አንድ እንደሆነ እና አብ የሚያደርገውን ሁሉ እንደሚያደርግ ለአይሁድ ሲነግራቸው ድንጋይ አንስተው ሊወግሩት በማሰባቸው ጌታችን ስለምን ትወግሩኛላቻሁ ባላቸው ጊዜ ስለመልካም ስራህ አንወግርህም ስለስድብህ ነው ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለማድረግህ ነው ማለታቸው በወንጌል ተመዝግቧል እንግዲህ አይሁድ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ማለቱ አምላክ ነኝ ማለቱ እንደሆነ ገብቷቸዋል ማለት ነው ዮሐ 10፡25-38

✧ ከዚህ ጥቅስ እንደምንረዳው ጌታችን ራሱን የእግዚአብሔር ልጅ ብሎ መጥራቱ አምላክ ነኝ ማለቱ እንደሆነ ነው/ ሙሉውን የአይሁድ እና የጌታን ንግግር አንብቡት/፡፡በሌላም ቦታ አይሁድ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎ ራሱን መጥራቱን ተቃውመው ሊገሉት እንደነበር የእግዚአብሄር ልጅ ነኝ ማለቱ ደግሞ እግዚአብሔር ነኝ ማለቱ እንደሆነ ተረድተውት ሊገሉት እንደሚፈልጉ ተገልጧል ‹‹እንግዲህ ሰንበትን ስለ ሻረ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ደግሞ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካክሎ <<
እግዚአብሔር አባቴ ነው ስላለ፥ ስለዚህ አይሁድ ሊገድሉት አብዝተው ይፈልጉት ነበር።››ዮሐ 5፡18

✧ ስናጠቃልለው ኢየሱስ እግዚአብሔር ልጅ ተብሎ መጠራቱ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደተመለከትነው አምላክ/እግዚአብሔር መሆኑን የሚገልጥልን ልጅነቱም ከማንም ያልተቀበለው ባህሪ ልጅነት እንደሆነ እግዚአብሄርንም የሚስተካከልበት ልጅነት በመልክ ሚመስልበት ልጅነት እንደሆነ ልንረዳ ያስፈልጋል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ሰላም የተዋህዶ እምነት ተከታዮች በሙሉ🙏

ከዛሬ ጀምሮ በአዲሱ ቻናላችን ስለ ሰ/ት/ቤቱ መረጃዎች እንዲሁም ስለተዋህዶ ሀይማኖት እየፃፍን እናቀርባለን።
ጎደኛዎትን ለመጋበዝ ከፈለጉ ከታች የለዉን ሰማያዊ ሊንክ ሼር በማድረግ አባልነቶን ያሳዩን።

@yeberhanljoche @yeberhanljoche
@yeberhanljoche @yeberhanljoche
💠 #ኢየሱስ_ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነው። 💠

✧ በወንጌልም ሆነ በተለያዩ የሀዲስ ኪዳን የመልእክት ክፍሎች ውስጥ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ተጠቅሶ ይገኛል። እንደውም ማንኛውም ክርስቲያን፥ ኢየሱስ እግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ማመን መቀበል እንዳለበት አጽንኦት ተሰጥቷል፡፡

✧ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቂሳርያ ሀዋርያቱን ሰብስቦ ሰዎች ማን እንደሚሉት በጠየቃቸው ጊዜ አንዳንዶች ኤልያስ ከነብያት አንዱ እንደሆነ እንደሚናገሩ ሲነግሩት እናንተ ማን እንደሆንኩ ትላላችሁ ብሎ ቢጠይቃቸው ክርስቶስ የህያው እግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ቅዱስ ጴጥሮስ ተናግሯል ጌታችንም ቅዱስ ጴጥሮስን አመስግኖ ስጋና ደም እንዳልገለጠለት የሰማዩ አባቱ እንደገለጠለት በመናገር በዚህ በቅዱስ ጴጥሮስ ንግግር ቤተክርስቲያኑን እንደሚመሰርት ጌታ ተናግሯል ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው የሚለው የቅዱስ ጴጥሮስ ንግግር የቤተክርስቲያን መሰረት ነው። የጌታን ማንነት የሚገልጽ እምነታችን መሰረት ነው፡፡

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ የማያምን እንዲሁም ብሎ የማይመሰክር ሰው ክርስቲያን ተብሎ ሊጠራ አይችልም ምክንያቱም የክርስትና መሰረት ይህ ስለሆነ ‹‹ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን። ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ። እርሱም፦ አንዳንዱ #መጥምቁ_ዮሐንስ ፥ ሌሎችም #ኤልያስ ፥ ሌሎችም #ኤርምያስ ወይም #ከነቢያት_አንዱ ነው ይላሉ አሉት።
እርሱም፦ #እናንተስ #እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው።
ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ፦ #አንተ #ክርስቶስ_የሕያው_እግዚአብሔር_ልጅ ነህ አለ። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ #በሰማያት ያለው #አባቴ እንጂ #ሥጋና #ደም ይህን #አልገለጠልህምና #ብፁዕ ነህ። እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም። የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል።››ማቴ 16፡13-19

ቅዱስ ገብርኤልም እመቤታችንን ለማብሰር በተላከ ጊዜ ከእርሷ የሚወለደው <<ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ>> እንደሚባል ነግሯታል እሷም ይህንን በእምነት ተቀብላ ስግው ቃል/ሰው የሆነ አምላክ/ እግዚአብሄርን በስጋ ወልዳዋለች ስለዚህም ወላዲተ አምላክ ብለን እንጠራታለን፡፡ የሉቃስ ወንጌል 1፡35 ‹‹መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት፦ መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።››

✧ በተለያየም ቦታ አጋንንት እኳን ሳይቀሩ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ መስክረዋል፡፡ ማቴ 8፡29 አይሁድም የእምነታችን መሰረት የሆነውን የእግዚአብሔር ልጅነቱን አልተቀበሉም ነበር፡፡ማቴ 26፡63 ይዘብቱበትም ነበር ማቴ 27፡43 ፡፡ ቅዱስ ማርቆስም ወንጌሉን ሲጀምር እግዚአብሔር ልጅነቱን መስክሮ ነው ማር1፡1፡፡ በተለያየ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል ክፍል ውስጥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑ ተጠቅሷል ይህንንም እናመን ዘንድ ወንጌል እንደተፃፈ ይነግረናል ዮሐ 1፡34 ፤1፡50 ፤6፡69 ፤ 10፡36 ፤11፡4 ፤11፡27 ፤ 19፡7 ፤ 20፡31፡፡

✧ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ይህንን አምኖ እንደተጠመቀ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል ሐዋ 8፡37፡፡ቅዱስ ዮሐንስ በመልእክቱም ኢሱስ የእግዚአብሄር ልጅ እንደሆነ ተናግሯል ‹‹ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በሚታመን ሁሉ እግዚአብሔር በእርሱ ይኖራል እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል።››1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4፡15፡፡

እንግዲህ ከላይ እንደተመለከትነው መጽሀፍቅዱስ አፅንኦት ሰጥቶ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በእግዚአብሔር ልጅነቱም ማመን እንዳለብን ይናገራል...

??? ለመሆኑ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ሲባል ምን ማለት ነው ???

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ሲባል መፅሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን እግዚአብሔር ነው ማለት ነው። እኛ የሰው ልጆች ሰዎች እንደምንባል ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ኢየሱስም እግዚአብሔር ተብሎ ይጠራል፡፡ ኢየሱስ እግዚአብሔር ነው ሲባል አብን በመልክ የሚመስለው በባህሪ የሚስተካከለው ማለታችን ነው ዮሐ 1፡1-3 ፤ ዮሐ 10 ፡30 ፤ዮሐ 14፡8-10 ‹‹እኔና አብ አንድ ነን እኔን ያየ አብን አይቷል››፡፡ ልጅነቱም የባህሪ ልጅነት ነው ማለትም ከማንም ያልተቀበለው ማንም የማይወስድበት ዘላለማዊ ልጅነት ነው፡፡

✧ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የአብ ልጅ እንደሆነ ከአብ ጋር አንድ እንደሆነ እና አብ የሚያደርገውን ሁሉ እንደሚያደርግ ለአይሁድ ሲነግራቸው ድንጋይ አንስተው ሊወግሩት በማሰባቸው ጌታችን ስለምን ትወግሩኛላቻሁ ባላቸው ጊዜ ስለመልካም ስራህ አንወግርህም ስለስድብህ ነው ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለማድረግህ ነው ማለታቸው በወንጌል ተመዝግቧል እንግዲህ አይሁድ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ማለቱ አምላክ ነኝ ማለቱ እንደሆነ ገብቷቸዋል ማለት ነው ዮሐ 10፡25-38

✧ ከዚህ ጥቅስ እንደምንረዳው ጌታችን ራሱን የእግዚአብሔር ልጅ ብሎ መጥራቱ አምላክ ነኝ ማለቱ እንደሆነ ነው/ ሙሉውን የአይሁድ እና የጌታን ንግግር አንብቡት/፡፡በሌላም ቦታ አይሁድ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎ ራሱን መጥራቱን ተቃውመው ሊገሉት እንደነበር የእግዚአብሄር ልጅ ነኝ ማለቱ ደግሞ እግዚአብሔር ነኝ ማለቱ እንደሆነ ተረድተውት ሊገሉት እንደሚፈልጉ ተገልጧል ‹‹እንግዲህ ሰንበትን ስለ ሻረ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ደግሞ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካክሎ <<
እግዚአብሔር አባቴ ነው ስላለ፥ ስለዚህ አይሁድ ሊገድሉት አብዝተው ይፈልጉት ነበር።››ዮሐ 5፡18

✧ ስናጠቃልለው ኢየሱስ እግዚአብሔር ልጅ ተብሎ መጠራቱ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደተመለከትነው አምላክ/እግዚአብሔር መሆኑን የሚገልጥልን ልጅነቱም ከማንም ያልተቀበለው ባህሪ ልጅነት እንደሆነ እግዚአብሄርንም የሚስተካከልበት ልጅነት በመልክ ሚመስልበት ልጅነት እንደሆነ ልንረዳ ያስፈልጋል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ሰላም የተዋህዶ እምነት ተከታዮች በሙሉ🙏

ከዛሬ ጀምሮ በአዲሱ ቻናላችን ስለ ሰ/ት/ቤቱ መረጃዎች እንዲሁም ስለተዋህዶ ሀይማኖት እየፃፍን እናቀርባለን።
ጎደኛዎትን ለመጋበዝ ከፈለጉ ከታች የለዉን ሰማያዊ ሊንክ ሼር በማድረግ አባልነቶን ያሳዩን።

@yeberhanljoche @yeberhanljoche
@yeberhanljoche @yeberhanljoche
​​​​እንኳን ለታላቁ ነቢይና ሰማዕት ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

#ቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ

ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነ ዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ6 የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: #ቅዱስ_ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል:: "#ዘካርያስ ካህኑና #ቅድስት_ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6)

¤የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል!

¤እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ 100 ደግሞ ደርሶ ነበር::

¤ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው የተነገረለት (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው::

¤ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል #እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው::

¤የአምላክ እናቱ ስትደርስና "#ሰላም" ስትላቸው መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ በሁዋላ ሰኔ 30 ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል::

¤ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ 2 ዓመት ከ6 ወር በሆነው ጊዜ #ሰብአ_ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ 'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" አሉ::

¤እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል:: አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ ለ3 (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ 5 (7) ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች:: ከሰማይ ዘካርያስና #ስምዖን ወርደው ቀበሯት::

¤ሕጻኑ ዮሐንስ ሲያለቅስ #ድንግል_ማርያም ስንት አገር አልፋ ሰማችው:: እርሷም ስደት ላይ ነበረችና:: ከጌታ ጋር በደመና ሒደው ድንግል አቅፋ አጽናናችው:: ጌታንም "እንውሰደው ይሆን?" አለችው:: ጌታችን ግን "ለአገልግሎት እስክጠራው እዚህ ይቆይ" አላት:: ባርካው: አጽናንታውም ተለያዩ::

¤ቅዱስ ዮሐንስ ከዚህ በሁዋላ በዚያ ቆላ የግመል ጠጉር ለብሶ: ጠፍር ታጥቆ ተባሕትዎውን ቀጠለ:: ለ25 (23) ዓመታትም በንጽሕና ሲኖር ከምድር አራዊትና ከሰማይ መላእክት በቀር ማንንም አላየም:: ይሕችን ዐመጸኛ ዓለምም አልቀመሳትም::

¤ከዚህ በሁዋላ 30 ዘመን ሲሞላው እግዚአብሔር ከሰማይ ተናገረው:: "ሒድ! የልጀን ጐዳና ጥረግ" አለው:: ነቢያት ስለዚህ ነገር ተናግረው ነበርና:: (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) አባቱ ዘካርያስም "ወአንተኒ ሕጻን ነቢየ ልዑል ትሰመይ: እስመ ተሐውር ቅድመ እግዚአብሔር ከመ ትጺሕ ፍኖቶ" (ሉቃ. 1:76) ብሎ መንገድ ጠራጊነቱን ተናግሮ ነበርና::

¤ቅዱስ ዮሐንስ በዚያ ጊዜ በኃይለ #መንፈስ_ቅዱስ እየገሰገሰ ከበርሃ ወደ ይሁዳ መጣ:: ያዩት ሁሉ ፈሩት: አከበሩት:: ቁመቱ ቀጥ ያለ: ጽሕሙ እንደ ተፈተለ ሐር የወረደ: ጸጉሩ የቁራ ያህል የጠቆረ: መልኩ የተሟላ: ግርማው የሚያስፈራ ገዳማዊ ነውና::

¤ፈጥኖም ሕዝቡን ለንስሃ ሰበከ:: ለንስሃም በርካቶችን አጠመቃቸው:: በዚህ አገልግሎት ለ6 ወራት ቆይቶ ጌታችን ወደ እርሱ ዘንድ መጣ:: ዮሐንስ ሰማይን ከነግሱ: ምድርን ከነ ልብሱ የያዘ ፈጣሪ 'አጥምቀኝ' ብሎ ሲመጣ ደነገጠ:: የሚገባበትም ጠፋው::

¤"እንቢ ጌታየ! አንተ አጥምቀኝ" አለው:: ጌታ ግን "ፈቅጄልሃለሁ" አለው:: አጠመቀው:: በዚህ ምክንያት ይሔው እስከ ዛሬም "#መጥምቀ_መለኮት" ሲባል ይኖራል:: ቅዱስ ዮሐንስ በመጨረሻ ሔሮድስን ገሰጸው:: ንጉሡም ተቀይሞ ለ7 ቀናት አሠረው::

¤በዚህች ቀንም ልደቱን ባከበረ ጊዜ ወለተ ሔሮድያዳ በዘፈን አጥምዳ አስማለችው:: እርሱም የታላቁን ነቢይ ራስ አስቆርጦ በወጪት አድርጐ ሰጣት:: አበው "እምሔሶ ለሔሮድስ ይብላዕ መሐላሁ - ሔሮድስ መሐላውን በበላ በተሻለው ነበር" ይላሉ:: የቅዱስ ዮሐንስ ራሱ በርራ ስትሔድ አካሉን ግን ደቀ መዛሙርቱ ቀብረውታል:: (ማቴ. 3:1, ማር. 6:14, ሉቃ. 3:1, ዮሐ. 1:6)

¤ርጉም ሔሮድስ አንገቱን ካስቆረጠው በሁዋላ የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ራሱ የጸጋ ክንፍ ተሰጥቷት ጌታችን ወዳለበት #ደብረ_ዘይት ሔዳ በፊቱ ሰገደች:: #ቅዱሳን_ሐዋርያት በአዩት ነገር ተገርመው ራሱን እጅ ነሷት::

¤ከዚሕ በሁዋላ ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ለቅዱስ ዮሐንስ ራስ የማስተማር ስልጣን ሰጥቶ አሰናበታት:: በመላው ዓለም ለ15 ዓመታት ስትሰብክ ኑራ በዚህች ቀን ዓረቢያ ውስጥ ዓርፋለች::

<<¤ አስማተ-ዮሐንስ መጥምቅ (የመጥምቁ ዮሐንስ ስሞች) ¤>>
1.ነቢይ
2.ሐዋርያ
3.ሰማዕት
4.ጻድቅ
5.ካሕን
6.ባሕታዊ/ገዳማዊ
7.መጥምቀ መለኮት
8.ጸያሔ ፍኖት (መንገድ ጠራጊ)
9.ድንግል
10.ተንከተም (የብሉይና የሐዲስ መገናኛ ድልድይ)
11.ቃለ አዋዲ (አዋጅ ነጋሪ)
12.መምሕር ወመገሥጽ
13.ዘየዐቢ እምኩሉ (ከሁሉ የሚበልጥ)

=>ጌታችን #መድኃኔ_ዓለም የመጥምቁ ዮሐንስን ምትረት አስቦ ይቅር ይበለን:: ጸጋውን: በረከቱንና ክብሩንም ያሳድርብን::
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
https://t.me/yeberhanljoche