EECMY Children Ministry: MY Sunday School
746 subscribers
894 photos
14 videos
169 links
MY Sunday School is the official page of EECMY Children Ministry.

Wholistic Growth For Our Children!

Access Sunday School learning materials at www.mysundayschool.org
Download Telegram
EECMY Children Ministry: MY Sunday School
ኢየሱስ  እና ማዕበሉ (ሉቃስ 8፣ማቴዎስ 8፣ ማርቆስ 4) YESUUSII FI BUBBEE JABAA (Luqaas 8, Maatewos 8, Maarqos 4) 👇 👇 👇 https://t.me/MYSundaySchool
ኢየሱስ  እና ማዕበሉ
(ሉቃስ 8፣ማቴዎስ 8፣ ማርቆስ 4)
===
ኢየሱስ ሲያስተምር ለመስማት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደ እርሱ ይመጡ ነበር፡፡ አንዳንዶች እርዳታውን ለመጠየቅ ይመጡ ነበር፡፡ አንዳንዶች ደግሞ ወደ መንግሥተ ሰማያት መግባት እንዴት እንደሚቻል ለመመር ይፈልጉ ነበር አንዳንድ የታመሙ ደግመሞ ጤናማ መሆን ይፈልጉ ነበር አንዳንድ ግዜ ኢየሱስ ምግብ ለመብላት እንኳጊዜ እስኪያጣ ድረስ ያጨናንቁት ነበር፡፡

ከአድካሚ ቀን በኋላ ኢየሱስ በገሊላ ባህር አጠገብ ነበር፡ ለማረፍ ፈለገ:: ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ‹‹ ከሕዝቡ ተለይተን ጥቂት ጊዜ ማረፍ አለብን›› አላቸው፡፡ ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ በታንኳ ተሳፍሪው ሐይቁን ማቋረጥ ጀመሩ ኢየሱስ በጀልባው የኋላ ክፍል ተኝቶ ነበር፡፡

ወዲያው ማዕበሉ ሐይቁን አናወጠው ሰማዩ ጠቆረ : ነፋሱም በኃይል መንፈስ ጀመረ ሞገዱ እየጨመረ መጣ: ጀልባው በውሃ ይሞላ ጀመር፡፡ ደቀመዛሙርቱ ፈሩ ያለጥርጥር ታንኳው ይሰምጣል ብለው አሰቡ፡፡

ኢየሱስን ቀሰቀሱትና ‹‹ጌታ ሆይ አድነን›› አሉት፡፡ ኢየሱስም በፍቅር ተመለከታቸው ‹‹ እኔ ሁልግዜ እንደምረዳችሁ አታውቁምን? ታዲያ ለምን ፈራችሁ? ብሎ ጠየቃቸው፡፡ ከዚያም ኢየሱስ ንፋሱንና ባሕሩን ‹‹ሰላም ይሁን ጸጥ በል›› ብሎ አዘዘው፡፡  ወዲያው ንፋሱም አቆመ፣ ባሕሩም ጸጥ አለ፡፡ ደቀ መዛመርቱ ‹‹ንፋሱንና ባሕሩ የሚታዘዝለት ኢየሱስ ማነው? ብለው ጠየቁ፡፡

ውድ ልጆች፡ ኢየሱስ ማዕበልና ንፋስም ሁሉ የሚታዘዙለት እውነተኛ እና ዘላለማዊ ጌታችን ነው፡፡ በህይወታችሁ ማንኛውም ዓይነት ማዕበል ሲያጋጥማችሁ አትፍሩ፡ ለጌታ ኢየሱስ ንገሩት፡ የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉ፡ እርሱ በነገር ሁሉ ይረዳችኋል፡፡
===
ውድ ልጆች: በሚቀጥሉት ጥያቄዎች ላይ ከወላጆቻችሁ ጋር ውይይት አድርጉ። መልካም እና የተባረከ ሳምንት ይሁንላችሁ!

ኢየሱስ ፍጹም ሰው መሆኑን የሚያሳይ ምን አደረገ?
ኢየሱስ አምላክ መሆኑን ለማሳየት ምን አደረገ?

This is the Official Channel of EECMY Children Ministry
#Follow #Forward #Share
https://t.me/MYSundaySchool
EECMY Children Ministry: MY Sunday School
ኢየሱስ  እና ማዕበሉ (ሉቃስ 8፣ማቴዎስ 8፣ ማርቆስ 4) YESUUSII FI BUBBEE JABAA (Luqaas 8, Maatewos 8, Maarqos 4) 👇 👇 👇 https://t.me/MYSundaySchool
YESUUSII FI BUBBEE JABAA
(Luqaas 8, Maatewos 8, Maarqos 4)

Namootni kumaatamni barsiisa Isaa dhaga’uuf gara Yesuus ni dhufan. Kaanimmoo gargaarsa Isa gaafachuuf dhufan. Namootni garri tokko attamitti mootummaa Waaqayyootti galuun akka danda’amu baruu barbaadan. Garri kaan immoo dhukkubsatoo waan turaniif fayyina barbaadu. Si’a tokko tokko namootni kun Yesuus hanga yeroo nyaataa dhabutti Isa muddaa turan.

Guyyaa dhiphaa sana booddee, Yesuus naannoo Galaana Galiilaa ture. Waan dadhabeef boqochuu ni barbaade. Yesuus duuka buutota Isaatiin akkas jedhe, “Kottaa me haroo kana gara gamatti ceenaa. Namoota kana irraa adda baanee yeroo xiqqoo boqochuu qabna.”

Yesuusii fi duuka-buutotni isaa bidiruu tokko yaabbatanii haroo sana ce’uu ni jalqaban. Yesuusis bidiricha gara duubaatiin ni rafe.

Yeroodhuma sana dhahaan galaanaa haroo sana irra bubbisuu jalqabe. Samiin ni gurraacha’e. Qilleensi ciminaan bubbise. Dhahaan bishaanii ol ka’aa adeeme. Bishaan bidirichatti guutuu jalqabe.
Duuka buutotni ni sodaatan. Isaan bidirichi dhugumatti ni liqimsama jedhanii yaadan.
Isaan Yesuusiin dammaqsanii akkas jedhan,”Gooftaa nu’oolchi!”

Yesuus gara-laafinaan gara firoota isaa ilaalee akkas jedhee isaan gaafate,”Maaliif sodaattani? Ani yeroo hundumaa iyyuu akkan isin gargaaru hin beektanii?”

Itti aansee Yesuus qilleensichaa fi dhaha galaanichatti dubbate. Akkasis jedhe, “Cal jedhi, Gab jedhi.”

Battalumatti qillensichi bubbisuu ni dhaabe, galaanicha irrattis gabiitu ta’e.

Duuka-buutotni Isaas akkas jedhanii gaafatan, “Yesuus kun eenyu? Qilleensii fi galaanni illee kan abboomamuuf.”

Yaa ijoollee, Yesuus Inni Gooftaa barabaraa qilleensii fi bubbeen kamuu abboomamuufiidha/ajajamuufiidha. Jireenya keessan keessatti qilleensii fi bubbeen kamuu yoo isin mudate hin sodaatinaa, hin dhiphatinaa. Gooftaa Yesuusitti himadhaa, Isatti dabarsaatii laadhaa. Inni waan isin dhiphisu kamuu isinirraa kaasa, rakkina keessan hundumaatti isin gargaara.
Ijoollee gaaffilee asii gadii kanneen irratti warra keessan waliin irratti mari’adhaa. Torbaan Gaarii isiniif haa ta’u!

1.  Yesuus eenyummaa isaa qabatamaa ta’e akka qabu wanta agarsiisu maal hojjete?
2.  Yesuus Waaqayyo akka ta’e agarsiisuudhaaf maal hojjate?

This is the Official Channel of EECMY Children Ministry
#Follow #Forward #Share
https://t.me/MYSundaySchool
ኢትዮጵያ በቅርቡ ከአውሮፓ ህብረት ጋራ የፈረመችውን ስምምነት በመቃወም የተዘጋጀ የፊርማ ማሰባሰቢያ ቅጽ
        * ⚠️ አስቸኳይ⚠️  *
ባሳለፍነው ህዳር 5 ቀን 2016 ዓም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ከካሪቢያንና ከፓሲፊክ የተውጣጡ ሀገራት ለሚቀጥሉት 20 ዓመታት የሚቆይ የንግድና ኢኮኖሚ ትብብር ስምምነትን ከአውሮፓ ህብረት ጋራ ሳሞዋ በምትባል ሀገር በፈረሙ ወቅት አገራችን ኢትዮጵያም ይህንኑ ስምምነት ተቀማጭነታቸው ብራሰልስ በሆኑ አምባሳደV አማካኝነት በፊርማዋ አጽድቃለች፡፡ ይህ አደገኛ ይዘቶች ያሏቸውን አንቀጾች የያዘው ስምምነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ ከሚቀጥለው ጥር ወር ጀምሮ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡

ይህ የትብብር ስምምነት በውሥጡ የያዛቸውን አስራ ሁለት ዋና ዋና አደገኛ ይዘቶችን ጠቅልለው የሚይዙ የተወሰኑ ሀሳቦች ለመጥቀስ ያህል ፡-

ሀ) የሀገር ሉዓላዊነትን የሚጥሱ አንቀጾች በግልጽ መቀመጣቸው፣

ለ) ግብረሰዶማዊነት፣ የጾታ መቀየርና፣¸ውርጃና ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርትን የመሳሰሉ እኩይ አጀንዳዎች በሰብዓዊ መብት ሽፋንና በሌሎች አሳሳች ሀረጎች ተሰውረው የገቡበት መሆኑ፣

ሐ) ግብረሰዶማዊነት በርካታ ቀውሶች ማለትም በአካል፣ በሥነልቦናና በማህበራዊ ህይወት ላይ የሚያስከትልና ለሀገር ደህንነትም አደጋ መሆኑ፣

መ) የወላጆችን መብት የሚጥስና የኢትዮጵያዊ ቤተሰብ እሴቶችን የሚንድ መሆኑ፣

ሠ) የሀገራችንን ሀይማኖት፣ባህልና እሴቶች የሚንዱ ጸያፍ ልምምዶችን እንድንቀበል በሰብዓዊ መብት ሽፋንና በእርዳታ ስም የምንገደድበትና ለዘመናዊ ባርነት ወይንም ቅኝ አገዛዝ ታልፈን የምንሰጥበት መሆኑ፣

በአጠቃላይ ይህ አዲስ የአጋርነት ስምምነት ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡና ትውልድንና ብሎም ሀገርን እጅግ የሚጎዱ በርካታ አንቀጾች የተካተቱበት መሆኑ ለሀገራችን ህዝብ ዕድገትን ሳይሆን ውድቀትንና ከፍተኛ የሞራል ዝቅጠትን የሚያስከትል መሆኑን በሚገባ ተረድተናል፡፡

በተጨማሪም ከተጠበቀው ውጭ ሀገራችን ይህንን ስምምነት በመፈረJ የተጋረጠብንን እጅግ አሳሳቢ አደጋ ለመቀልበስ አስፈላጊ የሆኑ ሰላማዊና ህጋዊ መንገዶችን ሁሉ በመጠቀም መንግስት ትኩረትን እንዲሰጠው ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡

በመሆኑም ይህ የመንግስት ውሳኔ እንደገና ተጠንቶ ውሳኔው እንዲቀለበስ ማለትም ስምምነቱ አስፈላጊው ሁሉ ማስተካከያ እስኪደረግበት ድረስ ወይንም እጅግ አደገኛ የሆኑት አንቀጾች ተነቅሰው ወጥተው የማንቀበላቸው መሆናችንን በይፋ ማሳወቅ (Submission of an Interpretive Declaration) እስከምንችል ድረስ የምንወዳት ሐገራችን ኢትዮጵያ ፊርማዋን በመሰረዝ ከስምምነቱ ራሷን እንድታገልል በሐገራችን ከፍተኛው የሥልጣን አካል ለሆነው ለተከበረው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለሐገሪቱ መሪ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በታላቅ አክብሮት እጅግ አስቸኳይ ጥሪን እናደርጋለን፡፡

የዚህንም ስምምነት አደገኛ አንቀጾችንና በኤክስፐርቶች የተሰጠውን ትንታኔ የያዘ ዶኩመንት በአባሪነት ያቀረብን መሆናችንንም በታላቅ አክብሮት እንገልጻለን፡፡


ፊርማውን ለመፈረም ሊንኩን ይጫኑ; አስፈላጊውን መረጃ ከሞላችሁ በኃላ 'አስገባ' የሚለውን ትጫናላችሁ... 'አስገባ' የሚለው ቀይ የነበረው ቀለም ወደ አርንጓዴ ሲቀየር ፈረማችሁ ማለት ነው::

ለሌሎችም እንዲደርስ #Share #Forward በማድረግ ተባበሩ!

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ: ይጠብቃትም!

https://keap.page/gq193//landing-page.html#appId=gq193;siteRef=bd460600-7d31-466c-8ab1-0f3f3cbd6ed0;pageRef=edad85db-899a-4ca1-a1ba-bf5db45dda57

#Ethiopia #Children #Youth #SaveGeneration #SaveTheChildren #SaveTheYouth