EECMY Children Ministry: MY Sunday School
746 subscribers
894 photos
14 videos
169 links
MY Sunday School is the official page of EECMY Children Ministry.

Wholistic Growth For Our Children!

Access Sunday School learning materials at www.mysundayschool.org
Download Telegram
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች ዛሬ መግለጫ አውጥተዋል።

መግለጫቸው ፤ በአውሮፓ ኅብረት እና በአፍሪካ፣ በካሪቢያንና በፓስፊክ ሀገራት መካከል የተፈረመውንና የሳሞአ ስምምነት በመባል የሚታወቀውን የንግድና የኢኮኖሚ አጋርነት ስምምነት የተመለከተ ነው።

ጉባኤው ስምምነቱ ተካተውበታል ያላቸውን ጎጂ ሀሳቦች በዝርዝር አስፍሯል።

ከነዚህም መካከል ፦

- በስምምነቱ አንቀፅ 36.2 ላይ የተጠቀሰው የወሲብና የተዋልዶ ጤናና መብቶች" ("Sexual and Reproductive Health and Rights") የሚለው ሐረግ በቀጥታ ፦
* #ከግብረሰዶም መብቶች፤
* ከፆታ መቀየር፤
* ከውርጃ፤
* ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርትና ግልሙትናን ሕጋዊ ከማድረግ በቀጥታ የተያያዘ መሆኑ በአውሮፓ ፓርላማና በዓለም የጤና ድርጅት የመረጃ ምንጮች ላይ በግልፅ መቀመጡ፤

- በስምምነቱ የአፍሪካ ፕሮቶኮል አንቀፅ 40.6 ላይ በአህጉሪቱ ለሚገኙ ልጆችና ታዳጊዎች ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርት (Comprehensive Sexuality Education) የተባለ እጅግ አደገኛ ኢግብረገባዊና ልቅ የወሲብ ትምህርት እንዲማሩ አስገዳጅ መሆኑ ለዚህም በዩኔስኮ የተዘጋጀውና እጅግ አደገኛ ይዘት እንዳለው የተረጋገጠው መተግበርያ "International Technical Guidance on Sexuality Education” በስም ተጠቅሶ መቀመጡ፤

- የፆታ ትንኮሳን (gender based violence) ማስቀረት በሚል በጣም አሻሚ የሆነ ግብረሰዶማዊ አስተሳሰቦችን ለማስረፅ እንዲረዳው በሰነዱ በበርካታ ክፍሎች ውስጥ " አካታች " (inclusive) በሚሉ ቃላት ተሸፍኖ እንዲገባ የተደረገ መሆኑ፤

- በበርካታ ሥፍራዎች የተጠቀሰው "Gender" የሚለው ቃል ወንድና ሴት ተብሎ እንደሚተረጎም በስምምነቱ በግልጽ ባለመቀመጡ ይልቁንም በርካታ ጾታዎች እንዳሉ በማስመሰል ሀገራትን የሚያደናግሩባቸው እንደ (sexual orientation እና gender identity)ን የመሳስሉ ግብረሰዶማዊ አስተሳሰቦችን የያዙ ዶክመንቶች በስም ተጠቅሰው በስምምነቱ ውስጥ መካተታቸው፤

- ስምምነቱ የወላጆችን መብት የሚጥስና የኢትዮጵያዊ ቤተሰብ እሴቶችን አደጋ ላይ የሚጥሉ አንቀፆችን የያዘ ስለመሆኑ በሰነዱ ላይ ከተደረገ የኤክስፐርቶች ጥልቅ ጥናት ተረድተናል...  የሚሉት ይገኙበታል።

ጉባኤው በነዚህ እና ሌሎች ጎጂ ምክንያቶች ፦

መንግስት የሳሞአ የንግድና የኢኮኖሚ የአጋርነት ስምምነትን በርካታ ጎጂ ጎኖች እንዳሉት በማመን ከዚህ ስምምነት #ኢትዮጵያ ራሷን እንድታገልል በማድረግ መንግስታዊ ኃላፊነቱንና አደራውን በተግባር እንዲወጣ በአጽንኦት ጠይቋል።

የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና በሥሩ ያሉ የሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች የስምምነት ሰነዱ ውስጥ በዝርዝር የቀረቡትን በተለይም ፦
° ከሰብኣዊ መብቶች፣
° ከወሲባዊና የተዋልዶ ጤናና መብቶች፣
° ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርት፤
° አካታችነት እና መሰል በሰነዱ የተካተቱ አንቀጾች ወይም ይዘቶች ከግብረሰዶማዊነትና ጾታን ከመቀየር እንዲሁም ከልቅ ወሲብና ከውርጃ ጋራ በቀጥታ ተያያዥነት ያላቸው ጽንስ ሃሳቦች መሆናቸውን በመረዳት ይህንን እጅግ አደገኛ ስምምነት ባለማጽደቅ ህዝባዊና ታሪካዊ አደራውን እንዲወጣ በአጽንኦት ጠይቋል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ስለ " ሳሞአ ስምምነት " ያዘጋጀው ሰፊ እና ዝርዝር ዘገባ በዚህ ይገኛል ፦ https://t.me/tikvahethiopia/84172

@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ በቅርቡ ከአውሮፓ ህብረት ጋራ የፈረመችውን ስምምነት በመቃወም የተዘጋጀ የፊርማ ማሰባሰቢያ ቅጽ
        * ⚠️ አስቸኳይ⚠️  *
ባሳለፍነው ህዳር 5 ቀን 2016 ዓም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ከካሪቢያንና ከፓሲፊክ የተውጣጡ ሀገራት ለሚቀጥሉት 20 ዓመታት የሚቆይ የንግድና ኢኮኖሚ ትብብር ስምምነትን ከአውሮፓ ህብረት ጋራ ሳሞዋ በምትባል ሀገር በፈረሙ ወቅት አገራችን ኢትዮጵያም ይህንኑ ስምምነት ተቀማጭነታቸው ብራሰልስ በሆኑ አምባሳደV አማካኝነት በፊርማዋ አጽድቃለች፡፡ ይህ አደገኛ ይዘቶች ያሏቸውን አንቀጾች የያዘው ስምምነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ ከሚቀጥለው ጥር ወር ጀምሮ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡

ይህ የትብብር ስምምነት በውሥጡ የያዛቸውን አስራ ሁለት ዋና ዋና አደገኛ ይዘቶችን ጠቅልለው የሚይዙ የተወሰኑ ሀሳቦች ለመጥቀስ ያህል ፡-

ሀ) የሀገር ሉዓላዊነትን የሚጥሱ አንቀጾች በግልጽ መቀመጣቸው፣

ለ) ግብረሰዶማዊነት፣ የጾታ መቀየርና፣¸ውርጃና ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርትን የመሳሰሉ እኩይ አጀንዳዎች በሰብዓዊ መብት ሽፋንና በሌሎች አሳሳች ሀረጎች ተሰውረው የገቡበት መሆኑ፣

ሐ) ግብረሰዶማዊነት በርካታ ቀውሶች ማለትም በአካል፣ በሥነልቦናና በማህበራዊ ህይወት ላይ የሚያስከትልና ለሀገር ደህንነትም አደጋ መሆኑ፣

መ) የወላጆችን መብት የሚጥስና የኢትዮጵያዊ ቤተሰብ እሴቶችን የሚንድ መሆኑ፣

ሠ) የሀገራችንን ሀይማኖት፣ባህልና እሴቶች የሚንዱ ጸያፍ ልምምዶችን እንድንቀበል በሰብዓዊ መብት ሽፋንና በእርዳታ ስም የምንገደድበትና ለዘመናዊ ባርነት ወይንም ቅኝ አገዛዝ ታልፈን የምንሰጥበት መሆኑ፣

በአጠቃላይ ይህ አዲስ የአጋርነት ስምምነት ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡና ትውልድንና ብሎም ሀገርን እጅግ የሚጎዱ በርካታ አንቀጾች የተካተቱበት መሆኑ ለሀገራችን ህዝብ ዕድገትን ሳይሆን ውድቀትንና ከፍተኛ የሞራል ዝቅጠትን የሚያስከትል መሆኑን በሚገባ ተረድተናል፡፡

በተጨማሪም ከተጠበቀው ውጭ ሀገራችን ይህንን ስምምነት በመፈረJ የተጋረጠብንን እጅግ አሳሳቢ አደጋ ለመቀልበስ አስፈላጊ የሆኑ ሰላማዊና ህጋዊ መንገዶችን ሁሉ በመጠቀም መንግስት ትኩረትን እንዲሰጠው ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡

በመሆኑም ይህ የመንግስት ውሳኔ እንደገና ተጠንቶ ውሳኔው እንዲቀለበስ ማለትም ስምምነቱ አስፈላጊው ሁሉ ማስተካከያ እስኪደረግበት ድረስ ወይንም እጅግ አደገኛ የሆኑት አንቀጾች ተነቅሰው ወጥተው የማንቀበላቸው መሆናችንን በይፋ ማሳወቅ (Submission of an Interpretive Declaration) እስከምንችል ድረስ የምንወዳት ሐገራችን ኢትዮጵያ ፊርማዋን በመሰረዝ ከስምምነቱ ራሷን እንድታገልል በሐገራችን ከፍተኛው የሥልጣን አካል ለሆነው ለተከበረው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለሐገሪቱ መሪ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በታላቅ አክብሮት እጅግ አስቸኳይ ጥሪን እናደርጋለን፡፡

የዚህንም ስምምነት አደገኛ አንቀጾችንና በኤክስፐርቶች የተሰጠውን ትንታኔ የያዘ ዶኩመንት በአባሪነት ያቀረብን መሆናችንንም በታላቅ አክብሮት እንገልጻለን፡፡


ፊርማውን ለመፈረም ሊንኩን ይጫኑ; አስፈላጊውን መረጃ ከሞላችሁ በኃላ 'አስገባ' የሚለውን ትጫናላችሁ... 'አስገባ' የሚለው ቀይ የነበረው ቀለም ወደ አርንጓዴ ሲቀየር ፈረማችሁ ማለት ነው::

ለሌሎችም እንዲደርስ #Share #Forward በማድረግ ተባበሩ!

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ: ይጠብቃትም!

https://keap.page/gq193//landing-page.html#appId=gq193;siteRef=bd460600-7d31-466c-8ab1-0f3f3cbd6ed0;pageRef=edad85db-899a-4ca1-a1ba-bf5db45dda57

#Ethiopia #Children #Youth #SaveGeneration #SaveTheChildren #SaveTheYouth